🔇Unmute
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለማምጣት ያላቸውን አቅም ማጠናከር እንዳለባቸው የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ገለፁ።
"ቀጣናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዓለምአቀፍ የምርምር ጉባኤ እየተካሄደ ነው።
በጉባኤው በቪዲዮ ኮንፍረንስ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በጥናትና ምርምር መደግፍ አለባቸው።

ለዚህም ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አስገንዝበዋል።
በተለይም ሀገረሰባዊ እውቀቶችን በምርምር በማስደገፍ በቀጣናው ሀገራትበዘመናዊ አስተዳድር ሥርአት ውስጥ የሚካተቱበትን አቅም መፍጠር ላይ ይበልጥ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸውዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለሀገርና ለቀጣናዊ ችግሮች መፍትሄ የሚሆኑ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ማበርከቱን ጠቅሰዋል።

የአየር ንብረት ለውጥ በቀጣናው እያደረሰ ያለውን ተጽዕኖ ለመከላከል ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያከናወነችው ተግባር በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ያሉት ደግሞ በኢትዮጵያ የግሎባል ግሪን ግሮውዝ ኢንስቲትዩት (GGGI) ተወካይ ኦኬቹኩ ዳንኤል ኦግቦናያ ናቸው።
የአፍሪካ ሕብረት በ2063 የሀይል፣ የውሀ ሀብትና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳን ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት የኢትዮጵያን ልምድ ሊቀስም ይገባል ሲሉም አመልክተዋል።

በካናዳ የዩርክ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሮፌሰር አሊ አስጋሪ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ አቅርቦትና ለአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እድገት የሰጠችው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በምርምር ጉባኤው በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ፣ በጤና፣ በትምህርትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ጥናቶች በተመራማሪዎች፣ በፖሊሲ አውጪዎችና ባለሙያዎች እየቀረቡ ነው።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026