የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

Apr 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለማምጣት ያላቸውን አቅም ማጠናከር እንዳለባቸው የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ገለፁ።

"ቀጣናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዓለምአቀፍ የምርምር ጉባኤ እየተካሄደ ነው።

በጉባኤው በቪዲዮ ኮንፍረንስ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በጥናትና ምርምር መደግፍ አለባቸው።


ለዚህም ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አስገንዝበዋል።

በተለይም ሀገረሰባዊ እውቀቶችን በምርምር በማስደገፍ በቀጣናው ሀገራትበዘመናዊ አስተዳድር ሥርአት ውስጥ የሚካተቱበትን አቅም መፍጠር ላይ ይበልጥ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።


የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸውዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለሀገርና ለቀጣናዊ ችግሮች መፍትሄ የሚሆኑ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ማበርከቱን ጠቅሰዋል።


የአየር ንብረት ለውጥ በቀጣናው እያደረሰ ያለውን ተጽዕኖ ለመከላከል ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያከናወነችው ተግባር በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ያሉት ደግሞ በኢትዮጵያ የግሎባል ግሪን ግሮውዝ ኢንስቲትዩት (GGGI) ተወካይ ኦኬቹኩ ዳንኤል ኦግቦናያ ናቸው።

የአፍሪካ ሕብረት በ2063 የሀይል፣ የውሀ ሀብትና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳን ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት የኢትዮጵያን ልምድ ሊቀስም ይገባል ሲሉም አመልክተዋል።


በካናዳ የዩርክ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሮፌሰር አሊ አስጋሪ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ አቅርቦትና ለአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እድገት የሰጠችው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በምርምር ጉባኤው በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ፣ በጤና፣ በትምህርትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ጥናቶች በተመራማሪዎች፣ በፖሊሲ አውጪዎችና ባለሙያዎች እየቀረቡ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026