የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ማዕከሉ እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ ነው

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 10/2017(ኢዜአ)፦ለትንሳኤ በዓል እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ እንደገለጹት፤ በኮሚሽኑ ሥር ባለው የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል አማካኝነት መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለህብረተሰቡ የተለያዩ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በተለያዩ የገበያ ማዕከላት በመሸጥ ላይ ይገኛል።


በተለይም ማዕከሉ ህብረተሰቡ ለበዓሉ የሚፈልጓቸውን የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንዲችል እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለህብረተሰቡም እየቀረቡ ካሉት ውስጥ የእርድ እንስሳት እና የእንስሳት ተዋጽኦዎች መካከል ዶሮ፣ ሰንጋ በሬዎች እና እንቁላል ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በመዲናዋ 117 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ላይ ከ451 ሺህ በላይ ዶሮዎች እና ከአምስት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን በላይ እንቁላል ለገበያ እየቀረበ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይም አቅርቦቱ እያደገ እንደሚሄድ አብራርተዋል።


በማዕከሉ እንደየመጠናቸው ከ80ሺህ ብር ጀምሮ ሰንጋዎች ለገበያ አቅርቦ እየሸጠ መሆኑን ጠቁመዋል።

ሴቶች አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል የመሸጫ ቦታ ላይ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች በመሸጥ ላይ መሆኑን ኢዜአ ለመመልከት ችሏል።


አቶ ፀጋዬ ጎብዴ ለአካባቢው ነዋሪዎች በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከማዕከሉ እንቁላል በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

እንቁላል ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።


የእንስሳት ተዋጽኦ ውስጥ ቅቤ በ800 ብር፣ አይብ 400 እና ወተት በሊትር 80 ብር ለገበያ አቅርበናል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ የሺወርቅ ዳኛቸው ናቸው።

ለበዓሉ እንቁላል ሲገበዩ ካገኘናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ወይዘሮ አስቴር አበበ እና ወይዘሮ አስካለ ትኩ በሰጡት አስተያየት ከማዕከሉ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆናቸውን ተናግረዋል።


በዚህም አንድ እንቁላል በ10 ብር ሂሳብ መግዛታቸውን ተናግረው፤ ይህም ከሌላው ቦታ ዋጋው ቅናሽ ያለው ነው ብለዋል።

በቀጣይም ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን እንዲገበያይ ተመሳሳይ ማዕከላት ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026