
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካና የአሜሪካ የግሉ ዘርፍ ትብብር ለጋራ ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሞሃመድ አሊ የሱፍ ተናገሩ።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከስፍራው እንደዘገበው ሊቀ-መንበሩ በአንጎላ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር የአሜሪካና የአፍሪካ የንግድና የኢንቨስትመንት ትብበር መጠናከር አለበት ብለዋል።
በሁለቱ ወገን ያለው የቢዝነስ ትስስር የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።
አፍሪካ አሁን ላይ ባላት ከፍተኛ የተፈጥሮና የሰው ሃብት እንዲሁም የፈጠራ ሥራ መስፋፋት ወሳኝ የለውጥ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው ይህንን ወደፊት ማስኬድ ይገባል ነው ያሉት።
አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ በተለያዩ ዘርፎች እንዲጎለብትና የአህጉሪቱ እድገት ቀጣይነት እንዲኖረው እየደገፈ መሆኑን ተናግረው ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ከዚህ አንጻር የአሜሪካ ኩባንያዎች በተለያዩ የአፍሪካ አገራት በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ጠይቀው፤ አሁን ላይ ከንግግር ባለፈ አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የጋራ ጥረትና ተግባር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በጉባኤው ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ሚኒስትሮች፣ የመንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣የሁለቱም ወገን የቢዝነስ መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026