
ሸካ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በሸካ ዞን በየኪ ወረዳ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት መርቀዋል።
በወረዳው አላሞ ቀበሌ የተገነባው ቡቢ አነስተኛ የመስኖ አውታር ከ66 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ800 በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል።
የክልሉ መንግስት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የመስኖ አውታሮችን ማስፋፋት ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው ብለዋል።

ይህም ክልሉ ያለውን የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀምና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል።
ባለፉት አራት ዓመታት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተገንብተው የእርሻ ሥራን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም ከ1 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት እንደተቻለ ተናግረዋል።
በቀጣይም የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሠራል ብለዋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክልሉና የዞን እንዲሁም የወረዳ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026