
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በክህሎት ልማት ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራትና ከአህጉራዊ ተቋማት ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።
ከፎረሙ በተጓዳኝ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ግሩፕ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።



የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለወጣቶች የክህሎት ልማት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ አበክራ እየሰራች ትገኛለች።
በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ተቋማዊ አድርጎ ከመተግበርና አሰራርን ከማመቻቸት አንጻር የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያም በክህሎት ልማት፣ በሥራ ገበያና መሰል ጉዳዮች ከአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ጋር ባለፉት ሶስት ዓመታት በጋራ ስትሰራ ቆይታለች ነው ያሉት።

በዛሬው እለት የተደረገው የመግባቢያ ስምምነትም ከድርጅቱ ጋር የሚሰሩ ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እና አህጉራዊ ትብብርን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል።
ድርጅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀጣናዊ ጽህፈት ቤት መክፈቱን ገልጸው፤ ይህም ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትስስር በማሳደግ በኩል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉዓለም ስዩም በበኩላቸው ተቋሙ በአፍሪካ ቀጣይነት ያለው የስራ እድል ፈጠራን ለማጎልበት እየሰራ ነው ብለዋል።

ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር የተደረገው ስምምነት በኢትዮጵያ የስራ እድል ፈጠራን ዘላቂነት ባለው መልኩ ለማስፋፋት የሚከናወኑ ስራዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል።
በፋይናንስ ዘርፍና የገበያ ትስስር መፍጠር ስራዎች ላይ የተቀናጀ ድጋፍ በማድረግ የንግድ ድርጅቶችን አቅምና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ድጋፍ እንደሚያደርግም አብራርተዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026