
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፡- በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ውጤቶች መመዝገባቸውን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ሲሆን በዛሬው ውሎው የክልሉን መንግስት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 ዕቅድ በመገምገም አፅድቋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ ከመድረኩ በኋላ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በብዙ መመዘኛዎች ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በምጣኔ ኃብት፣ በግብርና፣ በከተማ ልማት እንዲሁም የኢንዱስትሪና ሌሎች መስኮች የተገኙ ውጤቶችን በመዘርዘር በእንስሳት ሃብት ልማት፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በውሃ ልማትና ተደራሽነት፣ በትምህርትና ጤና ዘርፎች በርካታ ስራዎች መሰራታቸውንና ውጤቶችም መገኘታቸውን አብራርተዋል።
በክልሉ የመልካም አስተዳደር ጉዳይ በከፍተኛ ትኩረት እየተመራ ያለ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ እንደ ሀገር የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ረገድም በጥናት ላይ በመመስረት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አንስተው በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
ምክር ቤቱ ማምሻውን የክልሉን የ2018 ዓ.ም በጀት 32 ነጥብ 82 ቢሊዮን ብር ያፀደቀ ሲሆን በጀቱም ከክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌደራል መንግስት በሚሰጥ ድጎማና ከሌሎች የገቢ ምንጮች የሚሸፈን መሆኑ ተገልጿል።
የምክር ቤቱ ጉባኤ ነገም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በቀሪ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026