
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፡- በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ውጤቶች መመዝገባቸውን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ሲሆን በዛሬው ውሎው የክልሉን መንግስት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 ዕቅድ በመገምገም አፅድቋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ ከመድረኩ በኋላ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በብዙ መመዘኛዎች ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በምጣኔ ኃብት፣ በግብርና፣ በከተማ ልማት እንዲሁም የኢንዱስትሪና ሌሎች መስኮች የተገኙ ውጤቶችን በመዘርዘር በእንስሳት ሃብት ልማት፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በውሃ ልማትና ተደራሽነት፣ በትምህርትና ጤና ዘርፎች በርካታ ስራዎች መሰራታቸውንና ውጤቶችም መገኘታቸውን አብራርተዋል።
በክልሉ የመልካም አስተዳደር ጉዳይ በከፍተኛ ትኩረት እየተመራ ያለ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ እንደ ሀገር የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ረገድም በጥናት ላይ በመመስረት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አንስተው በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
ምክር ቤቱ ማምሻውን የክልሉን የ2018 ዓ.ም በጀት 32 ነጥብ 82 ቢሊዮን ብር ያፀደቀ ሲሆን በጀቱም ከክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌደራል መንግስት በሚሰጥ ድጎማና ከሌሎች የገቢ ምንጮች የሚሸፈን መሆኑ ተገልጿል።
የምክር ቤቱ ጉባኤ ነገም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በቀሪ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026