የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በዞኑ አርሶ አደሮች አሲዳማ አፈርን በማከም ምርታማነታቸውን ማሳደግ ችለዋል

Jul 21, 2025

IDOPRESS

ደብረማርቆስ፤ ሐምሌ 11 /2017(ኢዜአ)፡ - በምሥራቅ ጎጃም ዞን አርሶ አደሮች አሲዳማ አፈርን በኖራ አክመው የእርሻ ማሳቸውን በማልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻላቸው ተገለጸ።

ዘንድሮ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትኩረት ከተሰጠው ጉዳይ አሲዳማ አፈርን በማከም ማልማት እንደሆነ የዞኑ ግብርና መምሪያ አመልክቷል።

ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እስካሁን ከ48ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ በማቅረብ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ መበተኑን መምሪያው ጠቅሷል።

አርሶ አደር መልሳቸው ያዜ በዞኑ የማቻከል ወረዳ የቅዳማን ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ በአሲዳማ አፈር የተጠቃ አንድ ሄክታር የእርሻ ማሳቸውን በኖራ በማከም ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።

ይህም የመሬታቸውን ለምነት በመጨመሩ በሄክታር ከአምስት ኩንታል በላይ የምርት ጭማሪ ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።

በተያዘው የመኸር ወቅትም ተግባሩን ለማስቀጠል ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።

በአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ አርሶ አደር ተመስጌን ክብረት በበኩላቸው፤ ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በኖራ በማከም የአፈሩ ለምነት እንዲመለስ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ቀደም ሲል በአሲድ የተጠቃው ማሳቸው ምርቱ መቀነሱን አውስተው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተጠቃው ማሳቸው በኖራ አክመው በመዝራት የጤፍና የስንዴ ምርታቸው ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል።ያገኙትን ጥቅም ለማሳደግም ከዘር በፊት ቀደም ብለው ኖራ በመበተን ማከማቸውን አንስተዋል።

የምሥራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበበ መኮንን እንደገለጹት፤ ዘንድሮ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትኩረት ከተሰጠው ጉዳይ አሲዳማ አፈርን በማከም ማልማት ነው።


ለዚህም በዞኑ ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እስካሁን ከ48ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ በማቅረብ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ መበተኑን ተናግረዋል።

አርሶ አደሮችን በማሳተፍ እየተካሄደ ያለው አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ተግባር ውጤታማነቱ በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን አስረድተዋል።

ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመልክተው፤ በምሥራቅ ጎጃም ዞን በ2017/2018 የምርት ዘመን ከ642 ሺህ ሄክታር በላይ በሰብል ዘር በመሸፈን ከ25 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026