
አዲስ አበባ፤ሐምሌ14/2017(ኢዜአ)፡-የ2018 በጀት አመት ከተጠናቀቀው በጀት አመት የበለጠ ስኬት ለማስመዝገብ በትኩረት የምንሰራበት ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 በጀት አመት ውጤታማ ለሆኑ ተቋማት ዕውቅና እና ሽልማት አበርክቷል።
በዚህም ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች የመኪና እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ አፈጻጸም በማስመዝገብ ውጤታማ ሆኗል።
ውጤቱ የተገኘው ጠንክሮ በመስራት መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ ስኬት ያስመዘገቡትን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ለበለጠ ስራ እንዲተጉ አሳስበዋል።
ተቋማቱ የከተማዋ ልማት እንዲፋጠንና የነዋሪዎቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ጠንክረው መስራታቸውን አስታውቀዋል።
የዕውቅና መርኃ ግብሩ ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ይበልጥ የሚያበረታታ ሌሎችንም በቁጭት የሚያነሳሳ መሆኑን አንስተዋል።
የ2018 በጀት አመት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የምንሰራበት ነው ያሉት ከንቲባዋ፥ ዕውቅናው ለቀጣይ ስራ ስንቅ እንደሚሆን ነው ያስታወቁት።
ሽልማት እና ዕውቅና የተሰጣቸው ተቋማት፣ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በበኩላቸው፥ የተሰጣቸው እውቅናና ሽልማት በቀጣይ ጠንክረው በመስራት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን እንደሚያነሳሳቸው ገልጸዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026