የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ እና ጣሊያን የግብርና ትብብር ስምምነት ለምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ እና ጣሊያን የግብርና ትብብር ስምምነት ለምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በግብርናው ዘርፍ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እና የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ ተፈራርመዋል።


ስምምነቱ ኢትዮጵያ ምርታማነትን ለማሳደግ ለምታደርገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚጫወት ነው ተብሏል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ ስምምነቱ፥ የቡና ዕሴት ሰንሰለትን ማሳለጥ፣ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የቡና አምራች አርሶ አደሮችን መደገፍ እና የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ መሆኑን አስታውቀዋል።

ጣሊያን ዘመናዊ ግብርናን በመተግበር ከፍተኛ ተሞክሮ እንዳላት የጠቀሱት የግብርና ሚኒስትሩ፥ ስምምነቱ የስልጠና እና የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማካተቱን ተናግረዋል።

ጣሊያን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በግብርናው ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ይፋ ባደረገችው ዕቅድ መሰረት ኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሚያደርጋትን የመግባቢያ ስምምነት በቀዳሚነት መፈራረሟን አንስተዋል።

የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በትብብር 2ኛውን የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤን በስኬት ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ስምምነቱ ለሁለቱ ሀገራት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026