
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ እና ጣሊያን የግብርና ትብብር ስምምነት ለምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።
ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በግብርናው ዘርፍ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እና የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ምርታማነትን ለማሳደግ ለምታደርገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚጫወት ነው ተብሏል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ ስምምነቱ፥ የቡና ዕሴት ሰንሰለትን ማሳለጥ፣ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የቡና አምራች አርሶ አደሮችን መደገፍ እና የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጣሊያን ዘመናዊ ግብርናን በመተግበር ከፍተኛ ተሞክሮ እንዳላት የጠቀሱት የግብርና ሚኒስትሩ፥ ስምምነቱ የስልጠና እና የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማካተቱን ተናግረዋል።
ጣሊያን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በግብርናው ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ይፋ ባደረገችው ዕቅድ መሰረት ኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሚያደርጋትን የመግባቢያ ስምምነት በቀዳሚነት መፈራረሟን አንስተዋል።
የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በትብብር 2ኛውን የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤን በስኬት ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ስምምነቱ ለሁለቱ ሀገራት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026