
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ እና ጣሊያን የግብርና ትብብር ስምምነት ለምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።
ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በግብርናው ዘርፍ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እና የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ምርታማነትን ለማሳደግ ለምታደርገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚጫወት ነው ተብሏል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ ስምምነቱ፥ የቡና ዕሴት ሰንሰለትን ማሳለጥ፣ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የቡና አምራች አርሶ አደሮችን መደገፍ እና የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጣሊያን ዘመናዊ ግብርናን በመተግበር ከፍተኛ ተሞክሮ እንዳላት የጠቀሱት የግብርና ሚኒስትሩ፥ ስምምነቱ የስልጠና እና የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማካተቱን ተናግረዋል።
ጣሊያን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በግብርናው ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ይፋ ባደረገችው ዕቅድ መሰረት ኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሚያደርጋትን የመግባቢያ ስምምነት በቀዳሚነት መፈራረሟን አንስተዋል።
የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በትብብር 2ኛውን የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤን በስኬት ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ስምምነቱ ለሁለቱ ሀገራት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026