የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የመቱ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎችን በማፍለቅ የአካባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ እያደረገ ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤መስከረም 29/2018(ኢዜአ) :- የመቱ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎችን በማፍለቅ የአካባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገለጸ።

ዩኒቨርሲቲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያካሄዳቸው የምርምር ውጤቶች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ውይይት መካሄዱ ይታወሳል።

ዩኒቨርሲቲው ያካሄዳቸው የምርምር ውጤቶች የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርጉ በተለይም የሆርቲካልቸር፣ የእንስሳት ሀብት ልማትና የምርጥ ዘር ብዜት ላይ ያተኮሩ መሆናቸው ተገልጿል።


የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ የምርምርና ማሕበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት በድሉ ተካ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በግብርና፣ በጤናና በትምህርት ዘርፍ ያካሄዳቸውን የምርምር ውጤቶችን ለተጠቃሚ እያስተዋወቀ ይገኛል።

በተለይ በግብርናው ዘርፍ የፍራፍሬና የቡና ልማት ላይ እንዲሁም በእንስሳት ሀብት ልማት ደግሞ የወተት ላሞች ዝርያን በማሻሻል የወተት ምርትን ማሳደግ የሚያስቸሉ የምርምር ውጤቶች ይፋ ማድረጉን ተናግረዋል።


በተፈጥሮ ሀብት አጠባበቅ ዘርፍም ብዝሀ ህይወት እንዲጠበቅ ማህበረሰቡን ያሳተፉ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በጤና ዘርፍ ባሕላዊ መድኃኒቶችን በሳይንሳዊ መንገድ መጠቀም የሚያስችሉ አቅሞችን ለመፍጠር ጥናትና ምርምር ስራዎች እየተደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።


በተለይ በእጽዋት ላይ የተደረጉ የምርምር ስራዎች የአረንጓዴ አሻራና የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብርን ስኬታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን አክለዋል።

በሰብል ልማትና እንስሳት እርባታም በተለይ ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ያተኮሩ የምርጥ ዘር ግኝትና ብዜት ላይ ለሚሰራው ስራ አጋዠ ነውም ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶቹን በማስፋት በኢሉአባቦርና በቡኖ በደሌ ዞኖች እያሰራጨ እንደሚገኝ አመልክተው በቀጣይም የጥናትና ምርምር ስራዎቹን ከማጠናከረ ባለፈ በሰው ኃይል ልማት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026