🔇Unmute
መቱ ፤መስከረም 29/2018(ኢዜአ) :- የመቱ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎችን በማፍለቅ የአካባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገለጸ።
ዩኒቨርሲቲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያካሄዳቸው የምርምር ውጤቶች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ውይይት መካሄዱ ይታወሳል።
ዩኒቨርሲቲው ያካሄዳቸው የምርምር ውጤቶች የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርጉ በተለይም የሆርቲካልቸር፣ የእንስሳት ሀብት ልማትና የምርጥ ዘር ብዜት ላይ ያተኮሩ መሆናቸው ተገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ የምርምርና ማሕበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት በድሉ ተካ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በግብርና፣ በጤናና በትምህርት ዘርፍ ያካሄዳቸውን የምርምር ውጤቶችን ለተጠቃሚ እያስተዋወቀ ይገኛል።
በተለይ በግብርናው ዘርፍ የፍራፍሬና የቡና ልማት ላይ እንዲሁም በእንስሳት ሀብት ልማት ደግሞ የወተት ላሞች ዝርያን በማሻሻል የወተት ምርትን ማሳደግ የሚያስቸሉ የምርምር ውጤቶች ይፋ ማድረጉን ተናግረዋል።

በተፈጥሮ ሀብት አጠባበቅ ዘርፍም ብዝሀ ህይወት እንዲጠበቅ ማህበረሰቡን ያሳተፉ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በጤና ዘርፍ ባሕላዊ መድኃኒቶችን በሳይንሳዊ መንገድ መጠቀም የሚያስችሉ አቅሞችን ለመፍጠር ጥናትና ምርምር ስራዎች እየተደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተለይ በእጽዋት ላይ የተደረጉ የምርምር ስራዎች የአረንጓዴ አሻራና የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብርን ስኬታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን አክለዋል።
በሰብል ልማትና እንስሳት እርባታም በተለይ ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ያተኮሩ የምርጥ ዘር ግኝትና ብዜት ላይ ለሚሰራው ስራ አጋዠ ነውም ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶቹን በማስፋት በኢሉአባቦርና በቡኖ በደሌ ዞኖች እያሰራጨ እንደሚገኝ አመልክተው በቀጣይም የጥናትና ምርምር ስራዎቹን ከማጠናከረ ባለፈ በሰው ኃይል ልማት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026