የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የገቢ አሰባሰብን በውጤታማነት መምራት ጠንካራ ሀገር የመገንባት ህልማችንን ለማሳካት ወሳኝ ነው - አቶ አደም ፋራህ

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የገቢ አሰባሰብን በውጤታማነት መምራት ሁለንተናዊ ብልፅግናን በማፋጠን ጠንካራ ሀገር የመገንባት ህልማችንን ለማሳካት ወሳኝ ነው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለፁ።

የገቢዎች ሚኒስቴር ከፌዴራል የክልልና የከተማ አስተዳደር የገቢ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ጋር ከመስከረም 29 ቀን 2018 ጀምሮ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሲያካሂድ የቆየውን የውይይት መድረክ አጠናቋል።


አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በገቢ አሰባሰብ ላይ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል።

ለዚህም የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎችና የገቢ ተቋማት በዲጂታል የታገዘ የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያዎች ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል።

ታማኝ የግብር ከፋዮች እየተበራከቱ መምጣታቸው እንዲሁም የአመራሩ ክትትልና ድጋፍ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻላቸውን አንስተው ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


የግብር ከፋዮች የታክስ አከፋፈል እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸው አሁንም በአመለካከት ችግሮች ምክንያት የሚፈጠሩ የታክስ ስወራና ሌሎች ህገወጥ ስራዎችን መታገል ያስፈልጋል ነው ያሉት።

የታክስ አጣጣልና አሰባሰብ ስርዓት ውጤታማነት ለሀገራዊ ልማት መፋጠን ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው በማንሳት የገቢ ግብር አሰባሰቡን በውጤታማነት መምራት የግድ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም መፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ እንደሚያሳካ ጠቁመው ለዚህ ደግሞ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ማሳደግ ሚናው የላቀ ነው ብለዋል።

የፌደራልና የክልል የገቢ ዘርፍ አመራሮች ተልዕኳቸው ገቢ መሰብሰብ ብቻ ሳይሆን ተቋምና ሀገር መገንባት መሆኑን አውቀው ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026