የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በደሴ ከተማ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ በተያዘው ወር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

በደሴ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የዲጂታል አሰራርን ለማስፋት እየተደረገ ያለውን ጥረት በተመለከተ ኢዜአ የከተማ አስተዳደሩን ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝን አነጋግሯል።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በማብራሪያቸውም በከተማ አስተዳደሩ የህዝብን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተጠያቂነት ያለበት ለማድረግ የተቀናጀ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም የአገልግሎት እንግልትን ለማስቀረትና በአንድ ስፍራ ላይ በርከት ያሉ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

አገልግሎቱን በተያዘው ወር አጋማሽ ላይ ለመጀመርም የግንባታ ማስተካከያ፣ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ዝግጁ የማድረግ፣ የአገልግሎት መስጫ ግብዓቶችን የማሟላትና ብቁ የሰው ሃይል ዝግጁ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በማእከሉ በተለይም የመሬት ነክ፣ ገቢዎች፣ ንግድ፣ የቴሌኮም አገልግሎት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የባንክ፣ የኢሜግሬሽንና ሌሎችም አገልግሎቶች ተጀምረው እየሰፋ የሚሄድ ይሆናል ብለዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቃሲም አበራ፤ የሕብረተሰቡን የልማትና የአገልግሎት ፍላጎቶች መሰረት ያደረጉ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ የተቀላጠፈ ለማድረግ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት አገልግሎቱን ለማስጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲጀመር ለጊዜው በ39 የአገልግሎት አይነቶች ስራ የሚጀመር መሆኑን አንስተው አገልግሎቱ እየበዛና እየሰፋ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026