የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መገናኛ ብዙኃን ሕብረ ብሔራዊ አንድነትንና ሀገራዊ ብልጽግናን የማስረጽ ተልዕኳቸውን መወጣት አለባቸው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙኃን ሕብረ ብሔራዊ አንድነትንና ሀገራዊ ብልጽግናን የማስረጽ ተልዕኳቸውን መወጣት እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት አስገነዘቡ፡፡

የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ማስጀመሪያ መርኃ ግብር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ተካሂዷል።


የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ በሀገራችን ያለው ጋዜጠኝነት ኢትዮጵያን መምሰል አለበት።

በኢትዮጵያ ያሉ የግልም ይሁኑ የህዝብ ወይም የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን በአራት ጉዳዮች ላይ ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም ብለዋል።

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ በማንኛውም መገናኛ ብዙሃን የሚሰራ ጋዜጠኛ ሊረሳው የማይገባ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

መገናኛ ብዙሃን የኢትዮጵያን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የሚያጠናክሩ፣ የህዝብን ትብብርና አንድነት የሚያሳዩ መሆን አለባቸው ብለዋል።

የወል ትርክትን መገንባት እና ኢትዮጵያ መበልጸግ አለባት የሚለውን ሀገራዊ የብልጽግና ዕሳቤ ታሳቢ አድርገው መስራት እንዳለባቸውም አፅንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን መገናኛ ብዙኃንን ለመደገፍና ለማብቃት ያደረገው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው፤ በኢትዮጵያ ፈቃድ የወሰዱ መገናኛ ብዙኃን ኢትዮጵያን መምሰል አለባቸው ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያን ማበልጸግ ዘመናትን የተሻገረ የልሂቃን ዕሳቤ መሆኑን ያነሱት አማካሪ ሚኒስትሩ፤ ጋዜጠኝነት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠበቅ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

መገናኛ ብዙኃን በሁሉም ህብረተሰብ ዘንድ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ብልጽግናን የማስረጽ ተልዕኳቸውን መወጣት እንዳለባቸው ነው ያስገነዘቡት፡፡

ብሔራዊ ጥቅምን፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን፣ የወል ትርክትና ሀገራዊ ብልፅግናን በማስረጽ ተልዕኳቸው ላይ ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም ብለዋል፡፡


የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የመገናኛ ብዙኃን ዘርፉ የሚጠይቀውን ስልት፣ ፈጠራና ብቃት ለማሟላት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡

ጋዜጠኝነት ተምሮ የሚገባበት ብቻ ሳይሆን በየጊዜው ብቃቱ የሚለካበት፣ የሙያ ፈቃድ የሚሰጥበትና የሚታደስበት መሆን አለበት ብለዋል፡፡

በመርኃ ግብሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃንና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026