የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቃቃው ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ መግባቷ ይታወቃል።

ገቢራዊ ከተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ መካከል የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ማሻሻያ አንዱ ነው።

ማሻሻያው የውጭ ምንዛሪ ስርዓቱን ገበያ መር ማድረጉን ተከትሎ በወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶችን ተጠቃሚ እያደረጋችው ይገኛል።

ለአብነትም ቡና፣ አበባ፣ ሰሊጥ፣ የቅባት እህሎች፣ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት ለውጭ ገበያ ለሚያቀርቡ አካላት ማሻሻያው ትልቅ እርምጃ ነው ተብሏል።

የኢትዮጵያ ስጋ አምራቶችና ላኪዎች ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ ከሊፋ ሁሴን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተለይ ለስጋ አምራችና ላኪዎች ትልቅ እድል ይዞ መጥቷል።

ማሻሻያው በተለይም ከውጭ ምንዛሪ ተመን ጋር ተያይዞ ማነቆ የነበሩ አሰራሮችን ማቃለል ማስቻሉን ገልጸዋል።

ማሻሻያው ከተደረገ በኋላ በወጪ ንግድ አፈፃፀም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ያስታወቁት ሰብሳቢው፤ አሁን ላይ የማህበሩን ገቢ 67 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ነው የገለጹት።

በዚህም ባለፉት ሶስት ወራት 5ሺህ ሜትሪክ ቶን የስጋ ምርት በመላክ ከ27 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኝቱን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ አበባና አትክልት አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ዘውዴ በበኩላቸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ ማነቃቃቱን ገልፀዋል።

ከማሻሻያው በኋላ በአበባ ልማትና ምርቱን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ዘርፉን ለማስፋፋት ዕድል እንደተፈጠረላቸው አስታውቀዋል።

ሪፎርሙ በተለይም ከሆርቲካልቸር ኢንዱስትሪው በቅሬታ ይነሱ የነበሩ አሳሪ ፖሊሲዎችን ለመቀየር ሰፊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልፀዋል።

ማሻሻያው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ምርቶችን መላክ የሚያስችል ነው ያሉት አቶ ቴዎድሮስ፤ የተወሰዱት እርምጃዎች ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ እያገዙ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም በገመገሙበት ወቅት ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከወጪ ንግድ ከ2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን መግለጻቸውም ይተዋሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026