የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በፎረሙ የሚሳተፉ እንግዶች ወደ ክልሉ መምጣት የክልሉን ቱሪዝም ለማነቃቃት ያግዛል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦በጣና ፎረም የሚሳተፉ እንግዶች ወደ ክልሉ መምጣት የክልሉን ቱሪዝም ለማነቃቃት እንደሚያግዝ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ።

የተለያዩ ሃገራት መሪዎችን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች የሚሳተፉበት 11ኛው የጣና ፎረም ‘’አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ስርዓት’’ በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ይሆናል።

የቢሮ ኃላፊው አቶ መልካሙ ፀጋየ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በፎረሙ ለሚሳተፉ እንግዶች የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት በባህር ዳር ከተማ ተደርጓል።

ለዚህም እንግዶቹ የሚያርፉባቸው ሆቴሎች የኢትዮጵያዊያንን ባህል በጠበቀ አግባብ አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

አገልግሎት አሰጣጡ እንግዶቹን የሚመጥን እንዲሆንም በባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በባህር ዳር በሚካሄደው ፎረም የሃገራት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ምሁራን እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ይጠበቃሉ።

እነዚሁ እንግዶች በፎረሙ ከመሳተፍ ባሻገር በቆይታቸው የክልሉን ባህል፣እሴትና ወግ የተላበሰ አገልግሎት እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል።

የፎረሙ ተሳታፊዎች ወደ ክልሉ መምጣትም ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው መነቃቃት የጎላ አስተዋጽኦ እንዳለው አብራርተዋል።

እንግዶቹ በሚሰጣቸው አገልግሎት ልክ ወደ መጡበት አካባቢ ተመልሰው ስለ ክልሉ የቱሪዝም ሁኔታ እንዲያስተዋውቁ በሚያስችል አግባብ ይስተናገዳሉ ብለዋል።

ለዚህም ከኤርፖርት ከሚደረግ አቀባበል ጀምሮ ቆይታቸውን ጨርሰው እስኪመለሱ የመስህብ ስፍራዎችን ጭምር እንዲጎበኙና የሚሸጡ የእደ ጥበብ ውጤቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ እንደሚደረግም አመልክተዋል።

እንግዶቹ በሚቆዩባቸው ጊዜያትም ማህበረሰቡ የኢትዮጵያን እንግዳ የመቀበል ባህል አጉልቶ በማሳየት ለፎረሙ መሳካት ሚናውን መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

በክልሉ ካሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች መካከል የሰሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣የላሊበላ ወቅር አብያተ ክርስቲያናት፣የጎንደር አብያተ መንግሥት፣ የአይጠየፍ አዳራሽ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ እና የጣና ገዳማት በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

የፎረሙ የመጀመሪያ ምዕራፍ በባህር ዳር ከተማ ጥቅምት 14 የሚካሄድ ሲሆን ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ ጥቅምት 15 እና 16/2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ መገለፁ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026