የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን ለማፋጠን መሰረት በሚጥሉት ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ የድርሻችንን እንወጣለን

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና /ቦንጋ ፤ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ)፡ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን ለማፋጠን መሰረት በሚጥሉት ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን የሆሳዕናና የቦንጋ ከተሞች ነዋሪዎች ገለፁ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርላማ ከህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የሚተገበሩት ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊም ሆነ ማህበራዊ መጻኢ ዕድል መወሰን የሚችሉ ናቸው ማለታቸው ይታወሳል።

ፕሮጀክቶቹ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ ዕድልን ከመፍጠር ባሻገር ምርትና ምርታማነትን በእጥፍ ሊያሳድጉ እንደሚችሉ መግለጻቸውም እንዲሁ።

በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሆሳዕናና የቦንጋ ከተሞች ነዋሪዎች እንዳሉት ፕሮጀክቶቹ ያላቸው ተስፋ የሚያጓጉ እና ኢትዮጵያን አሁን ካለችበት የዕድገት ደረጃ ወደ ከፍታ የሚወስዷት በመሆናቸው ለተግባራዊነታቸው የሚጠበቅባቸውን ለማድረግ ተዘጋጅተዋል፡፡

አስተያየታቸውን ከሰጡ በሆሳዕና ከተማ የቦብቾ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ቸርነት ሰዎሬ እንደገለፁት፤ መተባበር ለኢትዮጵያ ከድህነት የመውጫ አንዱ መንገድ መሆኑን ከታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ተሞክሮ የተወሰደበት ነው፡፡

ይህም ኢትዮጵያ ሀብቷን በጋራ በማልማት የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች እውን በማድረግ የማንሰራራት ጉዞዋን ማፋጠን አንደሚቻል መረዳታቸውን ገልጸዋል፡፡

ሌላኛዋ የጀሎ ናረሞ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ አረጋሽ ካሳ በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን ከተባበርን ታሪክ መስራት እንደምንችል የሚያስረዱ ብዙ የታሪክና የልማት ተግባራት መኖራቸውን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለምክር ቤቱ ከሰጡት ማብራሪያም የሀገሪቱን የልማት ጉዞ የሚያሳልጡ የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የግብርና ልማቶች እንዲጠናከሩ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ በመጠቆም ፕሮጀክቶቹ የታለመላቸውን ግብ እንዲያሳኩ የሚጠበቅባቸውን ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የቦንጋ ከተማ ነዋሪው አቶ ክፍሌ አለሙ፤ የህዝብን የጋራ ጥቅሞች ለማሳካት በመንግስት የተያዙ ሜጋ ፕሮጀክቶች ከዳር እንዲደርሱ ሁላችንም በአንድነት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል ብለዋል።

የሀገርን ልማት እውን ለማድረግ ሁሉም በተባበረ ክንድ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባው በማመን ለተግባራዊነቱም የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ያስረዱት ደግሞ የቦንጋ ከተማ ነዋሪው አቶ እያዩ ገብረማርያም ናቸው፡፡

በመንግስት የታቀዱ ሜጋ ፕሮጀክቶች እውን መሆንም የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ በማፋጠን ለዜጎች ኑሮ መሻሻል ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል፡፡

የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅም ኢትዮጵያን ከድህነት በማላቀቅ ለትውልድ የሚሻገር ሃብት ለማፍራት የሚያስችል በመሆኑ በተፋጠነ መልኩ እውን እንዲሆኑም የሚጠበቅባቸውን ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.