የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በምእራብ ሸዋ ዞን በመኸር አዝመራ በ48 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የቢራ ገብስ ለምቷል

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ ፤ጥቅምት22/2018 (ኢዜአ)፡- በምእራብ ሸዋ ዞን በመኸር አዝመራ በ48 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የለማው የቢራ ገብስ እንክብካቤ እየተደረገለት ነው፡፡

በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የቢራ ገብስን በኩታ ገጠም በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው፡፡

በዚህም በዞኑ በስፋት ከሚመረተው የጤፍና ስንዴ ልማት በተጓዳኝ አርሶ አደሩ የቢራ ገብስ እንዲያመርት የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በመኸር አዝመራም በዘር ከተሸፈነው 48 ሺህ ሄክታር መሬት ከ1 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝም አስረድተዋል።

ምርታማነቱን ለማሳደግም የተሻሻሉ የቢራ ገብስ ዝርያዎችን ማቅረብ፣ የግብዓት አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግና በኩታ ገጠም የማደራጀት ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡

የቢራ ገብስ ልማቱ ወልመራ፣ አዳ በርጋ ፣ ጅባት፣ ጀልዱ፣ ድሬ እንጪኒ፣ ኤጄሬና ኤጀርሳ ለፎ ወረዳዎች በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘንድሮ የአየሩ ጸባይ ለእርሻው ተስማሚ በመሆኑ ምርቱ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው በልማቱ ከ29 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ እየሰራ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የቢራ ገብስ ምርታማነትን በሄክታር 37 ኩንታል ማድረስ መቻሉንም አስረድተዋል።

በአርሶ አደሮቹ ጥራቱን ጠብቆ የሚመረተው የቢራ ገብስ ለብቅል ፋብሪካዎች ግብዓት የሚውል ሲሆን ባለፈው ዓመትም የተሻለ ምርት መገኘቱን አስታውሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.