🔇Unmute
አምቦ ፤ጥቅምት22/2018 (ኢዜአ)፡- በምእራብ ሸዋ ዞን በመኸር አዝመራ በ48 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የለማው የቢራ ገብስ እንክብካቤ እየተደረገለት ነው፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የቢራ ገብስን በኩታ ገጠም በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው፡፡
በዚህም በዞኑ በስፋት ከሚመረተው የጤፍና ስንዴ ልማት በተጓዳኝ አርሶ አደሩ የቢራ ገብስ እንዲያመርት የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በመኸር አዝመራም በዘር ከተሸፈነው 48 ሺህ ሄክታር መሬት ከ1 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝም አስረድተዋል።
ምርታማነቱን ለማሳደግም የተሻሻሉ የቢራ ገብስ ዝርያዎችን ማቅረብ፣ የግብዓት አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግና በኩታ ገጠም የማደራጀት ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡
የቢራ ገብስ ልማቱ ወልመራ፣ አዳ በርጋ ፣ ጅባት፣ ጀልዱ፣ ድሬ እንጪኒ፣ ኤጄሬና ኤጀርሳ ለፎ ወረዳዎች በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ዘንድሮ የአየሩ ጸባይ ለእርሻው ተስማሚ በመሆኑ ምርቱ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው በልማቱ ከ29 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ እየሰራ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የቢራ ገብስ ምርታማነትን በሄክታር 37 ኩንታል ማድረስ መቻሉንም አስረድተዋል።
በአርሶ አደሮቹ ጥራቱን ጠብቆ የሚመረተው የቢራ ገብስ ለብቅል ፋብሪካዎች ግብዓት የሚውል ሲሆን ባለፈው ዓመትም የተሻለ ምርት መገኘቱን አስታውሰዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026