🔇Unmute
አምቦ ፤ጥቅምት22/2018 (ኢዜአ)፡- በምእራብ ሸዋ ዞን በመኸር አዝመራ በ48 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የለማው የቢራ ገብስ እንክብካቤ እየተደረገለት ነው፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የቢራ ገብስን በኩታ ገጠም በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው፡፡
በዚህም በዞኑ በስፋት ከሚመረተው የጤፍና ስንዴ ልማት በተጓዳኝ አርሶ አደሩ የቢራ ገብስ እንዲያመርት የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በመኸር አዝመራም በዘር ከተሸፈነው 48 ሺህ ሄክታር መሬት ከ1 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝም አስረድተዋል።
ምርታማነቱን ለማሳደግም የተሻሻሉ የቢራ ገብስ ዝርያዎችን ማቅረብ፣ የግብዓት አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግና በኩታ ገጠም የማደራጀት ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡
የቢራ ገብስ ልማቱ ወልመራ፣ አዳ በርጋ ፣ ጅባት፣ ጀልዱ፣ ድሬ እንጪኒ፣ ኤጄሬና ኤጀርሳ ለፎ ወረዳዎች በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ዘንድሮ የአየሩ ጸባይ ለእርሻው ተስማሚ በመሆኑ ምርቱ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው በልማቱ ከ29 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ እየሰራ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የቢራ ገብስ ምርታማነትን በሄክታር 37 ኩንታል ማድረስ መቻሉንም አስረድተዋል።
በአርሶ አደሮቹ ጥራቱን ጠብቆ የሚመረተው የቢራ ገብስ ለብቅል ፋብሪካዎች ግብዓት የሚውል ሲሆን ባለፈው ዓመትም የተሻለ ምርት መገኘቱን አስታውሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025