🔇Unmute
ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡- መንግስት የባሕር በር ማግኘትን የሕልውና ጉዳይ ማድረጉን በመደገፍ የድርሻችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን ሲሉ የባሕርዳር ከተማ ወጣቶች እና ሴቶች ገለጹ።
ኢዜአ በባሕርዳር ከተማ ያነጋገራቸው ወጣቶች እና ሴቶች በሰጡት አስተያየት፤ መንግስት የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አጀንዳ ማድረጉ የሚበረታታና የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ሳለዓምላክ አድማሱ፤ አይነኬ የነበረው የባሕር በር ጥያቄ በለውጡ መንግስት መነሳቱ ያጣነውን መብት ለማስከበር ከፍተኛ መነሳሳትን ፈጥሯል ብሏል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት ሁለተኛ ሀገር እንደመሆኗ ከባሕር በር ተገልላ የሚፈለገውን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ አዳጋች ያደርገዋል ነው ያለው።
ይህም የወጣቱን ተጠቃሚነት በእጅጉ የሚጎዳ መሆኑን ጠቅሶ፤ አሁን እንደ ሀገር የተነሳው የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ በዘርፉ ኢኮኖሚ ቀጥታ የመጠቀም ተስፋችንን ያለመለመ ነው ሲል ገልጿል።
የባሕር በር አጀንዳው በፍጥነት እንዲሳካ ሰላምን ከመጠበቅ ጀምሮ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ማድረግ ይገባናል ነው ያለው።
የባሕር በር አጀንዳ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁሉ ሀገራችን በጀመረችው መንገድ እንደሚሳካ ጥርጥር እንደሌለው የተናገረችው ደግሞ ትዕግስት አባቡ ናት።
ከውጭ ሀገራት ጋር ያለንን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የባሕር በር ጉዳይ ወሳኝ በመሆኑ በመንግስት የተሰጠው ትኩረት የሚደነቅና የሚበረታታ መሆኑን ገልጻለች።
መንግስት የባሕር በር ማግኘትን የሕልውና ጉዳይ ማድረጉን በመደገፍ የድርሻችን መወጣት ይጠበቅብናል ብላለች።
ሌላው አስተያየት ሰጪ ብርሃኑ አበበ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያ በሕዝብ ቁጥር ብዛት፣ ቀጣናዊ አዋሳኝነቷ፣ ሕጋዊ ማዕቀፎችና ታሪካዊ ዳራዎች የባሕር በር የመጠቀም መብት እንዳላት የተረጋገጠ ነው ብሏል።
በዚህም የተጀመረውን ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ ይበልጥ በማጠናከር በሕጋዊ መንገድ የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን መረባረብ ይገባናል ነው ያለው።
የባሕር በር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ይበልጥ በማነቃቃት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው እድገት ለማስመዝገብ የጎላ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሶ፤ ለወጣቶችና ሴቶች የስራ እድል በመፍጠርም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ያሳድጋል ብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሳባ ከምክር ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ማንሳታቸው ይታወሳል።
እንደ ሀገር የባሕር በር አጀንዳ ወሳኝ መሆኑን በማመን ይሕን ለማሳካትም አስፈላጊው ሁሉ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026