የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መንግስት የባሕር በር ማግኘትን የሕልውና ጉዳይ ማድረጉን በመደገፍ የድርሻችንን እንወጣለን

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡- መንግስት የባሕር በር ማግኘትን የሕልውና ጉዳይ ማድረጉን በመደገፍ የድርሻችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን ሲሉ የባሕርዳር ከተማ ወጣቶች እና ሴቶች ገለጹ።

ኢዜአ በባሕርዳር ከተማ ያነጋገራቸው ወጣቶች እና ሴቶች በሰጡት አስተያየት፤ መንግስት የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አጀንዳ ማድረጉ የሚበረታታና የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ሳለዓምላክ አድማሱ፤ አይነኬ የነበረው የባሕር በር ጥያቄ በለውጡ መንግስት መነሳቱ ያጣነውን መብት ለማስከበር ከፍተኛ መነሳሳትን ፈጥሯል ብሏል።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት ሁለተኛ ሀገር እንደመሆኗ ከባሕር በር ተገልላ የሚፈለገውን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ አዳጋች ያደርገዋል ነው ያለው።

ይህም የወጣቱን ተጠቃሚነት በእጅጉ የሚጎዳ መሆኑን ጠቅሶ፤ አሁን እንደ ሀገር የተነሳው የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ በዘርፉ ኢኮኖሚ ቀጥታ የመጠቀም ተስፋችንን ያለመለመ ነው ሲል ገልጿል።

የባሕር በር አጀንዳው በፍጥነት እንዲሳካ ሰላምን ከመጠበቅ ጀምሮ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ማድረግ ይገባናል ነው ያለው።

የባሕር በር አጀንዳ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁሉ ሀገራችን በጀመረችው መንገድ እንደሚሳካ ጥርጥር እንደሌለው የተናገረችው ደግሞ ትዕግስት አባቡ ናት።

ከውጭ ሀገራት ጋር ያለንን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የባሕር በር ጉዳይ ወሳኝ በመሆኑ በመንግስት የተሰጠው ትኩረት የሚደነቅና የሚበረታታ መሆኑን ገልጻለች።

መንግስት የባሕር በር ማግኘትን የሕልውና ጉዳይ ማድረጉን በመደገፍ የድርሻችን መወጣት ይጠበቅብናል ብላለች።

ሌላው አስተያየት ሰጪ ብርሃኑ አበበ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያ በሕዝብ ቁጥር ብዛት፣ ቀጣናዊ አዋሳኝነቷ፣ ሕጋዊ ማዕቀፎችና ታሪካዊ ዳራዎች የባሕር በር የመጠቀም መብት እንዳላት የተረጋገጠ ነው ብሏል።

በዚህም የተጀመረውን ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ ይበልጥ በማጠናከር በሕጋዊ መንገድ የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን መረባረብ ይገባናል ነው ያለው።

የባሕር በር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ይበልጥ በማነቃቃት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው እድገት ለማስመዝገብ የጎላ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሶ፤ ለወጣቶችና ሴቶች የስራ እድል በመፍጠርም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ያሳድጋል ብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሳባ ከምክር ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ማንሳታቸው ይታወሳል።

እንደ ሀገር የባሕር በር አጀንዳ ወሳኝ መሆኑን በማመን ይሕን ለማሳካትም አስፈላጊው ሁሉ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026