🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር እና የሳዑዲ አረቢያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባለስልጣን(ሞንሻት) የስትራቴጂካዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል።
የሳዑዲ አረቢያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባለስልጣን(ሞንሻት) ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ፎረም (BIBAN 2025 forum) ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል።
“የዓለም የእድሎች መዳረሻ” በሪያድ እየተካሄደ የሚገኘው ፎረም ዋና መሪ ሀሳብ ነው።

በፎረሙ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር ከሳዑዲ አረቢያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባለስልጣን(ሞንሻት) ስትራቴጂካዊ አጋርነት መስርቷል።
የአጋርነት ስምምነቱን የተፈራሙት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሳሚያ አብዱልቃድር እና የሳዑዲ አረቢያ ኢንተርፕራይዝ ባለስልጣን የአጋርነት ዘርፍ ዋና ስራ አስኪያጅ አብዱልሞህሴን ሳሌም አልሳሌም ናቸው።
በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር(ዶ/ር) እና የሳዑዲ አረቢያ ኢንተርፕራይዝ ባለስልጣን አስተዳዳሪ ሳሚ ኢብራሂም አልሁሴይኒ ተገኝተዋል።

አጋርነቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ስራ ፈጣሪዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእውቀት ሽግግር እና በገበያ ተደራሽነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ማጠናከርን ያለመ ነው።
ወጣት መር፣ ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ እድገት በማረጋገጥ የቀጣናውን የጋራ ግቦች ለማሳካት እንደሚያግዝም ተመላክቷል።
የሳዑዲ አረቢያ ኢንተርፕራይዝ ባለስልጣን የስራ ፈጣሪዎችን አቅም ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጾ ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ለማጠናከርና ሀገሪቱ ለስራ ፈጣሪ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የገበያ እድሎችን ለመፍጠር ያላትን ራዕይ ለማሳካት እንደሚሰራ አመልክቷል።
ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ፎረም (BIBAN 2025 forum) ነገ ይጠናቀቃል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026