የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ ልትገነባ ነው  

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ ልትገነባ ነው።

አካዳሚው የሚገነባው በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ ሲሆን፤ ግንባታው በ62 ሄክታር መሬት ላይ ያርፋል።


የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው፤ በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ከሁሉም አጎራባች ሀገሮች ጋር የሚያስተሳስሩ ዘመናዊ የባቡር መሠረተ ልማቶችን ከመዘርጋት ጎን ለጎን ኢንዱስትሪውን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስትራቴጂ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።


ለባቡር ኢንዱስትሪው የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት ተተኪ ባለሙያዎችን የማሰልጠን ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የሚገነባው የባቡር አካዳሚ ግንባታው ሲጠናቀቅ የኢንዱስትሪውን ተደራሽነት ለማስፋት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ለአጎራባች አገራት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን በመስጠት የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ እንደሚያገለግልም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው በበኩላቸው፤ የባቡር ትራንስፖርት የወጪ እና ገቢ ምርቶችን እንቅስቃሴን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳልጥ ተናግረዋል።


አካዳሚው ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ቀጣናውን በትምህርት ዲፕሎማሲ እንደሚያስተሳስር ተናግረዋል።

የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ እንደገለጹት፤ አካዳሚው ለከተማዋ በረከትና ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ሆኖ ያገለግላል።

በመሆኑም አካዳሚው በተቀመጠለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026