🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ ልትገነባ ነው።
አካዳሚው የሚገነባው በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ ሲሆን፤ ግንባታው በ62 ሄክታር መሬት ላይ ያርፋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው፤ በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ከሁሉም አጎራባች ሀገሮች ጋር የሚያስተሳስሩ ዘመናዊ የባቡር መሠረተ ልማቶችን ከመዘርጋት ጎን ለጎን ኢንዱስትሪውን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስትራቴጂ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።

ለባቡር ኢንዱስትሪው የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት ተተኪ ባለሙያዎችን የማሰልጠን ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሚገነባው የባቡር አካዳሚ ግንባታው ሲጠናቀቅ የኢንዱስትሪውን ተደራሽነት ለማስፋት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
ለአጎራባች አገራት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን በመስጠት የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ እንደሚያገለግልም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው በበኩላቸው፤ የባቡር ትራንስፖርት የወጪ እና ገቢ ምርቶችን እንቅስቃሴን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳልጥ ተናግረዋል።

አካዳሚው ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ቀጣናውን በትምህርት ዲፕሎማሲ እንደሚያስተሳስር ተናግረዋል።
የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ እንደገለጹት፤ አካዳሚው ለከተማዋ በረከትና ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ሆኖ ያገለግላል።
በመሆኑም አካዳሚው በተቀመጠለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025