የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ቡናን እሴት ጨምሮ በመላክ ለላቀ ስኬት መትጋት ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫችን ነው 

Nov 26, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦ቡናን በጥሬው ብቻ ሳይሆን እሴት ጨምሮ በመላክ ለላቀ ስኬት መትጋት ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለ2017 እቅድ አፈጻጸም መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት የእውቅና መርኃ ግብር አከናውኗል።


በመርኃ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ከለውጡ በፊት የቡና ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት ባለማግኘቱ እና በበርካታ ውስብስብ ችግሮች የተነሳ ለኢኮኖሚው የሚፈለገውን ገቢ ሳያመነጭ መቆየቱን አስታውሰዋል።


የመደመር መንግሥት ለአረንጓዴ ልማትና ለግብርና ዘርፍ በሰጠው ትኩረት ቡና አምራች አርሶ አደሮች የዕለት ፍጆታቸውን ከመሸፈን አልፈው ከፍተኛ ገቢ እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና በምታደርገው ጉዞ የምትከተለው የዕድገት መርህ አረንጓዴ የዕድገት አቅጣጫን መሠረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የአረንጓዴ ልማቱ ካሻሻላቸው ዘርፎች አንዱ የቡና ልማት እና ምርታማነት መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ቡናን ለዓለም ገበያ ማቅረብ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ፍጹም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበች መምጣቷን ጠቅሰዋል።


በ2017 በጀት ዓመት በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 470 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷን አንስተዋል።

ይህ ውጤት በመደመር መንግሥት አመራር፣በባለሙያዎች ሙያዊ ክትትል እና ጥረት እንዲሁም በአርሶ አደሮች ትጋት የተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም 600 ሺህ ቶን ቡና በመላክ ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት መታቀዱን ገልጸው፤ በቀጣይ ርብርባችን ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።


በመንግስት በኩል የቡና ምርታማነትና ጥራት ለማሻሻል የሚያስችሉ ኢንሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ቡናን በጥሬው ብቻ ሳይሆን እሴት ጨምሮ በመላክ ለላቀ ስኬት መትጋት ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንም አመላክተዋል።

ባለድርሻ አካላትም የተያዘውን እቅድ እንደሚያሳኩ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.