የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኮሪደር ልማት ከተሞችን ለኑሮ ምቹ፣ ውብና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እያደረጋቸው ነው -የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተሞችን ለኑሮና ለሥራ ምቹ፣ ውብና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማስቻላቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ገለፀ።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን ለኢዜአ እንዳሉት መንግስት ከተሞችን ለዜጎች ኑሮ ምቹና ተስማሚ ከማድረግ ባለፈ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል።

በተለይም ከተሞችን ለህፃናት እና ለአረጋውያን ምቹ የማድረግ ስራ በስፋት በመከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም ከተሞች ያሏቸውን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ሃብቶች በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ የሚያስችሉ የልማት ስራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል።

እንዲሁም አረንጓዴ ስፍራዎችን ለማስጠበቅ፣ ያለአግባብ ታጥረው የቆዩ መሬቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።

በመሆኑም የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር ዘመናዊና ተወዳዳሪ ከተሞችን ለመገንባት የኮሪደር ልማቱ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማት ስራዎች በሁሉም ክልሎች ባሉ ከሰባ በላይ በሚሆኑ ከተሞች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በሁሉም የሀገሪቱ ከተሞች ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የልማት ስራዎቹ የከተሞቹን ገጽታ የሚቀይሩና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታቸው ከፍ ያለ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተሞችን ለኑሮና ለሥራ ምቹ ከባቢ እንዲኖራቸው እንዲሁም ውብና ማራኪ ገጽታ እንዲላበሱ ማድረጉን ጠቅሰው፣ ተወዳዳሪነታቸውም እያደገ መምጣቱን አንስተዋል።

ለአብነትም አዲስ አበባን ዘመናዊ፣ ውብና ተወዳዳሪ ከተማ በማድረግ ዓለም አቀፍ መድረኮችን ለማስተናገድ ግንባር ቀደም ተመራጭ እንድትሆን ማስቻሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.