🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በተያዘው የበጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየሠራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ የድንጋይ ከሰል ሀብት በስፋት መኖሩን አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅትም በዳውሮ እና ኮንታ ዞኖች የድንጋይ ከሰል የማምረት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ እንደ ክልል ያለውን የድንጋይ ከሰል መጠን በጥናት ለመለየት እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በ2018 የበጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት በማዕከላዊ ገበያ በኩል ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ለማቅረብ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት 82 ሺህ ቶን ማምረት መቻሉንም አስረድተዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተያዘው የበጀት ዓመት እስካሁን ባለው ሂደት ለ1 ሺህ 499 ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025