የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት ለገበያ ለማቅረብ እየተሠራ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በተያዘው የበጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየሠራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ የድንጋይ ከሰል ሀብት በስፋት መኖሩን አንስተዋል።


በአሁኑ ወቅትም በዳውሮ እና ኮንታ ዞኖች የድንጋይ ከሰል የማምረት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በአጠቃላይ እንደ ክልል ያለውን የድንጋይ ከሰል መጠን በጥናት ለመለየት እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

በ2018 የበጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን እሴት የተጨመረበት የድንጋይ ከሰል በማምረት በማዕከላዊ ገበያ በኩል ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ለማቅረብ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።


በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት 82 ሺህ ቶን ማምረት መቻሉንም አስረድተዋል።

በማዕድን ዘርፉ በተያዘው የበጀት ዓመት እስካሁን ባለው ሂደት ለ1 ሺህ 499 ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.