የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በቅርስ ጥበቃና አያያዝ ስኬታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ በመደመር መንግሥት እይታ በቅርስ ጥበቃና አያያዝ ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሀይሉ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሀይሉ፣ የኦሮሚያ ክልል የባህልና ቱሪዝም ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሰለሞን ታምሩ፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት የዓለም ቱሪዝም ቀንን አስመልክቶ በምስራቅ ባሌ ዞን የሚገኘውን የድሬ ሼኽ ሁሴን ታሪካዊ ቦታ ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሀይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶችን በማደስና በማልማት የቱሪዝም ማዕከል እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።


በዚህም ለረጅም ጊዜ ትኩረት ያልተሰጣቸውን ታሪካዊ ቦታዎች በማልማትና ነባሮቹን በተሻለ መልኩ በመጠገን ሃብታቸው በአግባቡ እንዲገለጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ከዚህም ባሻገር መዳረሻዎቹን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ የመንገድ፣ የሆቴል እና የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በመደመር መንግሥት እይታ በቅርስ ጥበቃና አያያዝ ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ ገልፀዋል።


በኢትዮጵያ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ ቅርሶች ቁጥር እንዲጨምር እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህ ረገድ በምስራቅ ባሌ ዞን የሚገኘውን የድሬ ሼኽ ሁሴን ታሪካዊ ቦታ በዩኔስኮ የጊዜያዊ ዝርዝር ውስጥ በማስገባት የዓለም ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።


የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሰለሞን ታምሩ በበኩላቸው፤ በክልሉ የሚገኙትን ቅርሶች ለመጠበቅ፣ ለማልማትና ለማስተዋወቅ ሰፊ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ትኩረት ከተሰጣቸው ቅርሶች መካከል በምስራቅ ባሌ ዞን የሚገኘው የድሬ ሼኽ ሁሴን ታሪካዊ ቦታ አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ወደ ድሬ ሼኽ ሁሴን ታሪካዊ መዳረሻ የሚወስድ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ይህም የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ፣ ቅርሱን ይበልጥ ለማልማት፣ ለማስተዋወቅና በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026