የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በመደመር መንግሥት እይታ የሰው ሃይል ግንባታ ላይ ትኩረት ተደርጓል

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት እይታ በሁለንተናዊ ዘርፍ ወደፊት ለመስፈንጠር የሰለጠነ የሰው ሃይል ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረጉን የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፤ የመደመር መንግሥት የነበሩ ጥንካሬዎችንና ክፍተቶችን በመለየት ጥንካሬዎችን በተሻለ መልኩ የሚያስቀጥልና ክፍተቶችን ደግሞ በዘላቂነት የሚቀርፍ እሳቤ ነው፡፡

የመደመር መንግሥት እሳቤ ምርትና ምርታማነት በሚፈለገው ፍጥነትና መጠን አለማደጉን ከኢኮኖሚ ስብራቶቻችን መካከል አንዱ አድርጎ ይቆጥራል ብለዋል፡፡

እሳቤው ይህንን ስብራት በዘላቂነት ለመጠገን በተለያዩ ዘርፎች ብቁ የሰው ሃይል መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ያምናል ነው ያሉት፡፡

የብልጽግና ራዕይን እውን ለማድረግ የሰው ሃይል ግንባታን ልክ እንደ ካፒታል እና የተፈጥሮ ሃብት ይመለከታል ብለዋል፡፡

የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ የማዕድን፣ የቱሪዝምና የሌሎች ዘርፎችን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተለያዩ የሙያ መስኮች የሰለጠ የሰው ሀይል መገንባት በእጅጉ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሰው ሃይል ግንባታ እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት በተለይም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን ደረጃቸውን የማስጠበቅና የማስፋፋት ስራ ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡

አዳዲስ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተዘጋጅተው ስራ ላይ መዋላቸውንም አመላክተዋል፡፡

የትምህርት ስርዓቱ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ለጥራት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም የዜጎችን ዓለም-አቀፍ ተወዳዳሪነት እያሳደገው እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በዚህም ወጣቶች ከሥራ ፈላጊነት በመላቀቅ ሥራ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረግ መጀመራቸውን ነው የጠቆሙት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.