🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት እይታ በሁለንተናዊ ዘርፍ ወደፊት ለመስፈንጠር የሰለጠነ የሰው ሃይል ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረጉን የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፤ የመደመር መንግሥት የነበሩ ጥንካሬዎችንና ክፍተቶችን በመለየት ጥንካሬዎችን በተሻለ መልኩ የሚያስቀጥልና ክፍተቶችን ደግሞ በዘላቂነት የሚቀርፍ እሳቤ ነው፡፡
የመደመር መንግሥት እሳቤ ምርትና ምርታማነት በሚፈለገው ፍጥነትና መጠን አለማደጉን ከኢኮኖሚ ስብራቶቻችን መካከል አንዱ አድርጎ ይቆጥራል ብለዋል፡፡
እሳቤው ይህንን ስብራት በዘላቂነት ለመጠገን በተለያዩ ዘርፎች ብቁ የሰው ሃይል መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ያምናል ነው ያሉት፡፡
የብልጽግና ራዕይን እውን ለማድረግ የሰው ሃይል ግንባታን ልክ እንደ ካፒታል እና የተፈጥሮ ሃብት ይመለከታል ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ የማዕድን፣ የቱሪዝምና የሌሎች ዘርፎችን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተለያዩ የሙያ መስኮች የሰለጠ የሰው ሀይል መገንባት በእጅጉ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሰው ሃይል ግንባታ እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት በተለይም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን ደረጃቸውን የማስጠበቅና የማስፋፋት ስራ ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡
አዳዲስ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተዘጋጅተው ስራ ላይ መዋላቸውንም አመላክተዋል፡፡
የትምህርት ስርዓቱ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ለጥራት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም የዜጎችን ዓለም-አቀፍ ተወዳዳሪነት እያሳደገው እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
በዚህም ወጣቶች ከሥራ ፈላጊነት በመላቀቅ ሥራ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረግ መጀመራቸውን ነው የጠቆሙት፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026