🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት እይታ በሁለንተናዊ ዘርፍ ወደፊት ለመስፈንጠር የሰለጠነ የሰው ሃይል ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረጉን የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፤ የመደመር መንግሥት የነበሩ ጥንካሬዎችንና ክፍተቶችን በመለየት ጥንካሬዎችን በተሻለ መልኩ የሚያስቀጥልና ክፍተቶችን ደግሞ በዘላቂነት የሚቀርፍ እሳቤ ነው፡፡
የመደመር መንግሥት እሳቤ ምርትና ምርታማነት በሚፈለገው ፍጥነትና መጠን አለማደጉን ከኢኮኖሚ ስብራቶቻችን መካከል አንዱ አድርጎ ይቆጥራል ብለዋል፡፡
እሳቤው ይህንን ስብራት በዘላቂነት ለመጠገን በተለያዩ ዘርፎች ብቁ የሰው ሃይል መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ያምናል ነው ያሉት፡፡
የብልጽግና ራዕይን እውን ለማድረግ የሰው ሃይል ግንባታን ልክ እንደ ካፒታል እና የተፈጥሮ ሃብት ይመለከታል ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ የማዕድን፣ የቱሪዝምና የሌሎች ዘርፎችን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተለያዩ የሙያ መስኮች የሰለጠ የሰው ሀይል መገንባት በእጅጉ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሰው ሃይል ግንባታ እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት በተለይም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን ደረጃቸውን የማስጠበቅና የማስፋፋት ስራ ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡
አዳዲስ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተዘጋጅተው ስራ ላይ መዋላቸውንም አመላክተዋል፡፡
የትምህርት ስርዓቱ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ለጥራት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም የዜጎችን ዓለም-አቀፍ ተወዳዳሪነት እያሳደገው እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
በዚህም ወጣቶች ከሥራ ፈላጊነት በመላቀቅ ሥራ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረግ መጀመራቸውን ነው የጠቆሙት፡፡
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026