🔇Unmute
ባሕር ዳር ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡- ባሕር ዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ ማዕከል ማድረግ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ ገለጹ።
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርና የሰሜን ጎጃም ዞን ሰልጣኝ መካከለኛ አመራሮች በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው።

አመራሮቹ የኢንዱስትሪ መንደርን፣ የኮሪደር ልማት፣ የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዮም፣ መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት መስጫና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው እንደሚጎበኙም ታውቋል።
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት፤ ባሕር ዳርን ለነዋሪዎቿ ምቹና ፅዱ ከተማ ለማድረግ የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በተለይ በከተማ አስተዳደሩ 268 የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች በስራ ላይ እንዳሉ ጠቅሰው፤ 108 ኢንዱስትሪዎች ደግሞ በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
እነዚህ ኢንዱስትሪዎች ተኪ ምርቶችን ከማምረት ባለፈ ለበርካታ ወገኖች የስራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ ሚናቸውን እየተወጡ ይገኛል ነው ያሉት።
እንዲሁም በመጀመሪያው ምዕራፍ የተገነባው የኮሪደር ልማት ከጣና ኃይቅ ጋር የሚያስተሳስሩ መንገዶች በመከፈታቸው የከተማዋ ውበት ይበልጥ የተገለጠበት መሆኑን ተናግረዋል።
እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ከተማዋ ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እንድትሆን እያስቻሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በመደመር መንግስት እይታ በመቃኘት የከተማዋን ዕድገትና ልማት በማፋጠን የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026