የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከክልሉ ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረበ ያለው የቡና ምርት መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 2/2018(ኢዜአ)፡- ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረበ ያለው የቡና ምርት መጠንና ጥራት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የክልሉ የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ባለሥልጣን ገለጸ።

ባለፉት አራት ዓመታት በየዓመቱ በአማካይ 52ሺህ 257 ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አሥራት መኩሪያ ለኢዜአ ተናግረዋል።

በ2018 በጀት ዓመትም 71ሺህ 400 ቶን የታጠበና ያልታጠበ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ እስካሁን 10ሺህ 21 ቶን ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን አረጋግጠዋል።


በአሁኑ ወቅትም የቀይ እሸት ቡና ምርት አሰባሰብና የታጠበ ቡና ምርት ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

የዘንድሮውን ዕቅድ ለማሳካት የቡና ግብይትና ዝውውር ሕጋዊ እንዲሆን ብሎም ጥራቱን ለማስጠበቅ በየደረጃው ያለው የቡና ምርት ጥራትና ግብይት ቁጥጥር ግብረ-ኃይል ክትትልና ቁጥጥር እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

የታጠበ ቡና ምርት አዘገጃጀትና ጥራት አጠባበቅን አስመልክቶ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በተግባር የተደገፈ ስልጠና መሰጠቱንም አንስተዋል።

በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ እስካሁን በቡና ችግኝ ዝግጅት፣ በቡና ምርት አሰባሰብና ምርት ዝግጅት ለ22 ሺህ 441 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.