🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 2/2018(ኢዜአ)፡- ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረበ ያለው የቡና ምርት መጠንና ጥራት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የክልሉ የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ባለሥልጣን ገለጸ።
ባለፉት አራት ዓመታት በየዓመቱ በአማካይ 52ሺህ 257 ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አሥራት መኩሪያ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በ2018 በጀት ዓመትም 71ሺህ 400 ቶን የታጠበና ያልታጠበ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ እስካሁን 10ሺህ 21 ቶን ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን አረጋግጠዋል።

በአሁኑ ወቅትም የቀይ እሸት ቡና ምርት አሰባሰብና የታጠበ ቡና ምርት ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
የዘንድሮውን ዕቅድ ለማሳካት የቡና ግብይትና ዝውውር ሕጋዊ እንዲሆን ብሎም ጥራቱን ለማስጠበቅ በየደረጃው ያለው የቡና ምርት ጥራትና ግብይት ቁጥጥር ግብረ-ኃይል ክትትልና ቁጥጥር እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
የታጠበ ቡና ምርት አዘገጃጀትና ጥራት አጠባበቅን አስመልክቶ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በተግባር የተደገፈ ስልጠና መሰጠቱንም አንስተዋል።
በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ እስካሁን በቡና ችግኝ ዝግጅት፣ በቡና ምርት አሰባሰብና ምርት ዝግጅት ለ22 ሺህ 441 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025