የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተስጥቷል

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በዚህም በክልሉ በበጋ መስኖ 4 ሺህ 482 ሄክታር መሬት በስንዴ እንደሚለማም ተመላክቷል።

ስንዴ አብቃይ ባልሆኑ አካባቢዎች ጭምር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በስፋት ተተግብሮ ውጤት እየተገኘበት ይገኛል።

የበጋ ስንዴ ልማቱ ውጤታማ ከሆነባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች መካከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዱ ሲሆን በልማቱም ተስፋ ሰጪ ለውጦች እየታዩ ነው።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ግዳልቅ አልቅሚ እንዳሉት በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት የተጀመረውን ሀገራዊ ኢንሼቲቭ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።

በተያዘው የበጋ መስኖ የግብርና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም በአርሶና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች 4 ሺህ 482 ሄክታር መሬት ሙሉ የግብርና ፓኬጅ በመጠቀም ይለማል ብለዋል።

በስንዴ ልማቱ 158 ሺህ 492 ኩንታል ምርት ለማግኘት ግብ መጣሉንም አቶ ግዳልቅ ተናግረዋል።

ከመደበኛ የስንዴ ልማቱ በተጨማሪ በመኸር እርሻ በአርሶ አደሮች ማሳ ጭምር የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት ሥራ መከናወኑን አስታውሰው ይህም የምርጥ ዘር አቅርቦትና ጥራት ችግርን በመፍታት የስንዴ ምርታማነትን ያሳድጋል ብለዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዘንድሮ የበጋ መስኖ ከስንዴ ልማቱ ባሻገር በተለያዩ ሰብሎች ከ150 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር በመሸፈን ከ38 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.