🔇Unmute
ጂንካ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በዚህም በክልሉ በበጋ መስኖ 4 ሺህ 482 ሄክታር መሬት በስንዴ እንደሚለማም ተመላክቷል።
ስንዴ አብቃይ ባልሆኑ አካባቢዎች ጭምር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በስፋት ተተግብሮ ውጤት እየተገኘበት ይገኛል።
የበጋ ስንዴ ልማቱ ውጤታማ ከሆነባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች መካከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዱ ሲሆን በልማቱም ተስፋ ሰጪ ለውጦች እየታዩ ነው።
ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ግዳልቅ አልቅሚ እንዳሉት በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት የተጀመረውን ሀገራዊ ኢንሼቲቭ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
በተያዘው የበጋ መስኖ የግብርና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም በአርሶና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች 4 ሺህ 482 ሄክታር መሬት ሙሉ የግብርና ፓኬጅ በመጠቀም ይለማል ብለዋል።
በስንዴ ልማቱ 158 ሺህ 492 ኩንታል ምርት ለማግኘት ግብ መጣሉንም አቶ ግዳልቅ ተናግረዋል።
ከመደበኛ የስንዴ ልማቱ በተጨማሪ በመኸር እርሻ በአርሶ አደሮች ማሳ ጭምር የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት ሥራ መከናወኑን አስታውሰው ይህም የምርጥ ዘር አቅርቦትና ጥራት ችግርን በመፍታት የስንዴ ምርታማነትን ያሳድጋል ብለዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዘንድሮ የበጋ መስኖ ከስንዴ ልማቱ ባሻገር በተለያዩ ሰብሎች ከ150 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር በመሸፈን ከ38 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025