🔇Unmute
ጂንካ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በዚህም በክልሉ በበጋ መስኖ 4 ሺህ 482 ሄክታር መሬት በስንዴ እንደሚለማም ተመላክቷል።
ስንዴ አብቃይ ባልሆኑ አካባቢዎች ጭምር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በስፋት ተተግብሮ ውጤት እየተገኘበት ይገኛል።
የበጋ ስንዴ ልማቱ ውጤታማ ከሆነባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች መካከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዱ ሲሆን በልማቱም ተስፋ ሰጪ ለውጦች እየታዩ ነው።
ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ግዳልቅ አልቅሚ እንዳሉት በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት የተጀመረውን ሀገራዊ ኢንሼቲቭ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
በተያዘው የበጋ መስኖ የግብርና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም በአርሶና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች 4 ሺህ 482 ሄክታር መሬት ሙሉ የግብርና ፓኬጅ በመጠቀም ይለማል ብለዋል።
በስንዴ ልማቱ 158 ሺህ 492 ኩንታል ምርት ለማግኘት ግብ መጣሉንም አቶ ግዳልቅ ተናግረዋል።
ከመደበኛ የስንዴ ልማቱ በተጨማሪ በመኸር እርሻ በአርሶ አደሮች ማሳ ጭምር የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት ሥራ መከናወኑን አስታውሰው ይህም የምርጥ ዘር አቅርቦትና ጥራት ችግርን በመፍታት የስንዴ ምርታማነትን ያሳድጋል ብለዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዘንድሮ የበጋ መስኖ ከስንዴ ልማቱ ባሻገር በተለያዩ ሰብሎች ከ150 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር በመሸፈን ከ38 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026