የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በዲጂታል ግብርና ላይ የጀመረችው ተግባር ለአፍሪካ የዲጂታል ግብርና ሽግግር በምሳሌነት የሚወሰድ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዲጂታል ግብርና ላይ የጀመረችው ተግባር ለአፍሪካ የዲጂታል ግብርና ሽግግር በምሳሌነት የሚወሰድ መሆኑን በአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማ፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አከባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ተናገሩ።

በአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማ፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የአፍሪካን የግብርና ስርዓት ለመለወጥና የምግብ ዋስትናን ለማረጋግጥ ዲጂታል ግብርናን መተግበር ወሳኝ ነው።

ይህም ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የምርት ብክነትን ለመቀነስ፣ የፋይናንስና የገበያ ተደራሽነትን ማስፋትን ጨምሮ የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ቁልፍ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የግብርና ዘርፉን በዲጂታል ስርዓት ለመቀየር የጀመረችው ጥረት አስደናቂ መሆኑን ገልጸዋል።

ዲጂታል ግብርና ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የምታደርገውን ጥረት ለማገዝ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራሞችን መሠረት በማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ለዲጂታል ሽግግርና ለዘመናዊ ግብርና ዕድገት ያላቸው አስተዋፅኦ የጎላ እንደሆነም ነው የተናገሩት።

የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞው በዘመናዊ አሰራሮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ተከትሎ ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት የስንዴ ምርትን በእጅጉ ማሳደግ መቻሏን አንስተዋል።

ውጤቱ የተገኘው በዲጂታል ስርዓት የታገዘ የአፈር ካርታ አሰራርና ሌሎች ዘመናዊ የግብርና ስልቶችን መጠቀም በመጀመሯ እንደሆነ ገልፀዋል።

በተጨማሪም አርሶ አደሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ስንዴና ካሳቫ የሚዘሩበትን አካባቢ በግልጽ ለማወቅ እያስቻላቸው ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ይህም የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በዲጂታል ግብርና የጀመረችው ተግባር ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ ተደርጎ የሚወሰድና ለአህጉሪቱ የግብርና ዘርፍ አዲስ ተስፋ የፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.