የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በትብብር ሥራችን ኢትዮጵያን ከዓለም ንግድ በማስተሣሠር ወደ ላቀ ብልጽግና እናሸጋግራለን!

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ዛሬ ሀገራችን ወደ ዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የምታደርገውን ጉዞና የድርድር ሂደት አስመልክቶ በተዘጋጀው ታላቅ መድረክ ተገኝተናል።

ኢትዮጵያ የበርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት መሥራች ብትሆንም፣ ከዓለም የንግድ ድርጅትና የትሥሥር ሂደት ለረጅም ጊዜ ባይተዋር ሆና ቆይታለች።


የመደመር መንግሥት በወሰደው ጠንካራ አመራርና ቁርጠኝነት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎቻችን ከሁለት ዐሠርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የአባልነት የድርድር ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

በተለይም ባለፉት ሰባት ወራት የተመዘገቡ ስኬቶች የድርድሩን መቋጫ የሚያሳዩ ናቸው።

የዓለም ንግድ ድርጅት አባል መሆናችን የገበያ ተደራሽነትን ያሰፋልናል፤ የንግድና ኢንቨስትመንት ግልጽነትና ተገማችነትን በማጎልበት ተመራጭነታችንን ያሳድጋል።


የድርድሩን ሂደት በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ መንግሥት በቁርጠኝነት ይሠራል። ሂደቱ ቅንጅትን የሚሻ በመሆኑ የግሉ ዘርፍ፣ አስፈጻሚ ተቋማት ሚናቸውን እንዲወጡ ዓለም አቀፍ አጋሮችም ድጋፍቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ -

ምክትል ጠቅላይ ሚነኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.