🔇Unmute
ዛሬ ሀገራችን ወደ ዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የምታደርገውን ጉዞና የድርድር ሂደት አስመልክቶ በተዘጋጀው ታላቅ መድረክ ተገኝተናል።
ኢትዮጵያ የበርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት መሥራች ብትሆንም፣ ከዓለም የንግድ ድርጅትና የትሥሥር ሂደት ለረጅም ጊዜ ባይተዋር ሆና ቆይታለች።

የመደመር መንግሥት በወሰደው ጠንካራ አመራርና ቁርጠኝነት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎቻችን ከሁለት ዐሠርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የአባልነት የድርድር ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
በተለይም ባለፉት ሰባት ወራት የተመዘገቡ ስኬቶች የድርድሩን መቋጫ የሚያሳዩ ናቸው።
የዓለም ንግድ ድርጅት አባል መሆናችን የገበያ ተደራሽነትን ያሰፋልናል፤ የንግድና ኢንቨስትመንት ግልጽነትና ተገማችነትን በማጎልበት ተመራጭነታችንን ያሳድጋል።

የድርድሩን ሂደት በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ መንግሥት በቁርጠኝነት ይሠራል። ሂደቱ ቅንጅትን የሚሻ በመሆኑ የግሉ ዘርፍ፣ አስፈጻሚ ተቋማት ሚናቸውን እንዲወጡ ዓለም አቀፍ አጋሮችም ድጋፍቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ -
ምክትል ጠቅላይ ሚነኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026