የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ መሠረተ ልማቶች ነዋሪውን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በመቱ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሠረት ልማት ግንባታዎች የነዋሪውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለጹ።

ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ኦልጂራ ሒርኪሳ እንዳሉት፤ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉት የመንገድ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት የነዋሪውን የልማት ጥያቄ የሚመልሱ ናቸው።


የፕሮጀክቶቹ መገንባት ለዜጎች የስራ ዕድሎች የፈጠሩና የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ለቱሪስት መስህብነት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆኑ አክለዋል።

የመቱ የከተማ ነዋሪው አቶ ታከለ ጌትነት በበኩላቸው፤ በከተማዋ ቀደም ባሉት አመታት ተሰርተው በእድገቷ ልክ ባለ መታደሳቸውና በአዲስ የተጀመሩትም በወቅቱ ባለመጠናቀቃቸው ለነዋሪው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው መቆየታቸውን አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን ከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር ለመቅረፍ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የጀመራቸው ስራዎች ለህብረተሰቡ የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ምላሽ መስጠታቸውን ተናግረዋል።

እሳቸውም ከከተማዋ አስተዳደር ጋር በመተባበር ለከተማዋ እድገት የበኩላቸውን እያበረከቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።


የመቱ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ከበደ ነገሱ እንደተናገሩት፤ የከተማዋን ነዋሪ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቷል።


ለአብነትም በበጀት ዓመቱ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ቀደም ሲል የተጀመሩና በአዲስ መልክ እየተገነቡ የሚገኙ 44 ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ ወደ ስራ ለማስገባት ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በከተማዋ ከሚገነቡት ፕሮጀክቶች መካከል የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ ጤና ጣቢያ፣ የተቀናጀ የከተማ ግብርና፣ ቡኡረ-ቦሩ እና መደበኛ ትምህርት ቤቶች፣ የገበያ ማዕከል፣ ሼዶችና የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እንደሚገኙበት አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.