🔇Unmute
መቱ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በመቱ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሠረት ልማት ግንባታዎች የነዋሪውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለጹ።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ኦልጂራ ሒርኪሳ እንዳሉት፤ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉት የመንገድ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት የነዋሪውን የልማት ጥያቄ የሚመልሱ ናቸው።

የፕሮጀክቶቹ መገንባት ለዜጎች የስራ ዕድሎች የፈጠሩና የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ለቱሪስት መስህብነት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆኑ አክለዋል።
የመቱ የከተማ ነዋሪው አቶ ታከለ ጌትነት በበኩላቸው፤ በከተማዋ ቀደም ባሉት አመታት ተሰርተው በእድገቷ ልክ ባለ መታደሳቸውና በአዲስ የተጀመሩትም በወቅቱ ባለመጠናቀቃቸው ለነዋሪው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው መቆየታቸውን አንስተዋል።
በአሁኑ ወቅት ግን ከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር ለመቅረፍ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የጀመራቸው ስራዎች ለህብረተሰቡ የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ምላሽ መስጠታቸውን ተናግረዋል።
እሳቸውም ከከተማዋ አስተዳደር ጋር በመተባበር ለከተማዋ እድገት የበኩላቸውን እያበረከቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የመቱ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ከበደ ነገሱ እንደተናገሩት፤ የከተማዋን ነዋሪ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቷል።

ለአብነትም በበጀት ዓመቱ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ቀደም ሲል የተጀመሩና በአዲስ መልክ እየተገነቡ የሚገኙ 44 ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ ወደ ስራ ለማስገባት ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በከተማዋ ከሚገነቡት ፕሮጀክቶች መካከል የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ ጤና ጣቢያ፣ የተቀናጀ የከተማ ግብርና፣ ቡኡረ-ቦሩ እና መደበኛ ትምህርት ቤቶች፣ የገበያ ማዕከል፣ ሼዶችና የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እንደሚገኙበት አክለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026