የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ተሻግረው በአፍሪካ ገበያ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸውን አበርክቶ ይበልጥ በማጠናከር ከኢትዮጵያ ተሻግረው በአፍሪካ ገበያ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ‎መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡

በ2014 የተቋቋመው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 41 የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ወደ አንድ በመሰብሰብ የኢትዮጵያን ሃብት የማወቅ፣ ተበታትኖ የቆየውን ሃብት በተደራጀ መንገድ የማስተዳደር ስራ ተግባራዊ እየሆነ ይገኛል።

ተቋሙ ከመመስረቱ አስቀድሞ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የፋይናንስ፣ የኦዲት፣ የካፒታል፣ የብድር ጫና እና የኮርፖሬት አስተዳደር ችግር ውስጥ የነበሩ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚብሩክ ታዬ (ዶ/ር) አስታውሰዋል።

አሁን ላይ በኢትዮጵያ ኢንቨትመንት ሆልዲንግስ ስር የሚገኙ የልማት ድርጅቶች ዘመናዊ የባለቤትነት፣ የአስተዳደር ስርዓት እና ዓለም አቀፍ የኮርፖሬት አስተዳደር ስርዓት ተዘርግቶላቸዋል ብለዋል። በተጨማሪም ዘመናዊ የኦዲት ስርዓት እንዲከተሉ መደረጉንም አስታውቀዋል።

‎‎ይህም ተቋማቱ ከኪሳራ ወጥተው ወደ ትርፋማነት እንዲሸጋገሩ አስችሏል ነው ያሉት። ባለፉት አራት ዓመታትም የተቋማቱ አጠቃላይ ገቢ ቀድሞ ከነበረበት ከ704 ቢሊየን ብር ወደ 6.1 ትሪሊየን ብር ማሳደግ መቻሉን ጠቁመዋል።

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ዛሬ ላይ በ36 ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

በአጠቃላይ በእነዚህ ተቋማት ስር ያለው የሃብት መጠንም 8.2 ትሪሊየን ብር መድረሱን አስታውቀዋል።

በዚህም የመንግስት የልማት ድርጅቶች በኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸውን አበርክቶ ይበልጥ በማጠናከር ከኢትዮጵያ ተሻግረው በአፍሪካ ገበያ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ነው ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.