🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦በቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች አዳዲስ ኦፕሬተሮችን ወደ ስራ ከማስገባት ጀምሮ የኔትወርክ ተደራሽነት እና የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል ሲሉየኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርባልቻ ሬባ (ኢንጅነር) ገለጹ፡፡
ቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ ለሃገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የሚያስችል ተቋማዊ አሰራርን መከተል ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
ለዚህም በዘርፉ የሚሰማሩ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ መስጠት፣ መከታተልና መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርባልቻ ሬባ (ኢንጅነር) ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ዘርፉ በራሱ እድገት እንዲያስመዘግብ ከማድረግ ባለፈ ለሌሎች ዘርፎች እድገት አስቻይ በመሆኑ በትኩረት እየሰራ ይገኛልም ብለዋል።
አሁን ላይ በዘርፉ የተደረጉ ማሻሻያዎች አዳዲስ ኦፕሬተሮችን ወደ ስራ ከማስገባት ጀምሮ የኔትወርክ ተደራሽነት እና የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል።
ይህ ዘርፍ በራሱ ከሚያስመዘግበው ውጤት ባለፈ ለሌሎች ዘርፎች አስቻይ በመሆኑ በዘርፉ ላይ የሚሰራው ስራ ወሳኝ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
በተለይ ቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፉ ለፋይናንስ ተደራሽነት፣ ቅልጥፍና እና ዘመናዊ አገልግሎት እየሰጠው ያለው አገልግሎት ተጠቃሽ ነው ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026