የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በከተማዋ የቱሪስት ፍሰትና የቆይታ ጊዜን የሚያሳድጉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ የቱሪስት ፍሰትን ለመጨመርና የቆይታ ጊዜን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ገለጸ።

በባህር ዳር ከተማ ጣና ሃይቅ ለ9ኛ ዙር የታንኳ ቀዘፋ ውድድርና የጀልባ ትርኢት እየተካሄደ ይገኛል።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ጋሻው እንዳለው እንደገለጹት፤ "የጥርን በባህር ዳር" መርሃ ግብር ልዩ ልዩ ኹነቶች የከተማዋን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እያሳደገው ይገኛል።


የዚሁ አካል የሆነው የጣና ላይ የታንኳ ቀዘፋ ውድድር እና የጀልባ ትርኢት የከተማዋን የቱሪስት ፍሰት ለማሳደግና የቆይታ ጊዜን ለማራዘም ማገዙንም አክለዋል።

"ጥርን በባህር ዳር " አካል የሆነው በጣና ላይ የሚከናወነው የታንኳ ቀዘፋ ውድድር ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ እየሆነ መጥቷል ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ የቱሪስቱን ፍሰት በመጨመርና የዘርፉን አቅም ለማሳደግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን መደገፍ እንዲሁም የኮሪደር ልማት ማከናወኑን አንስተዋል።


የባህር ዳር ከተማን የቱሪስት ፍሰት በመጨመርና የዘርፉን አቅም ለማሳደግ መሰል ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህር ዳር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ ብርሃን ንጉሴ በበኩላቸው፤ የከተማዋን ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በፍጥነትና በጥራት በማከናወን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።


በተለይም የኮሪደር ልማት ስራዎች የባህር ዳር ከተማን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።

"ጥርን በባህር ዳር" መርሃ ግብር አካል የሆነው የጣና ላይ የታንኳ ቀዘፋ ውድድር እና የጀልባ ትርኢት የከተማዋ የቱሪዝም ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያድግ ማገዙን ጠቁመዋል።

ውድድሩን ይበልጥ በማስተዋወቅ ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ለማድረግና የመንግስታቱ ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) እንዲመዘገብ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መስራት ይገባል ብለዋል።

በውድድር ስነ ስርዓቱ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና የከተማው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026