🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 14/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የከተሞች ትራንስፎርሜሽንን የልማት እቅዷ ማዕከል ማድረጓ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አርአያ የሚሆን ነው ሲሉ የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ የከተሞች ከፍተኛ ዳይሬክተር ሄስቲንግስ ቺኮኮ ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያን የከተሞች የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ለማፋጠንና የከተሞችን የሀብት ማሰባሰብ አቅም ማሳደግ የሚያስችል ስልታዊ ስምምነት ተፈረመ።
ስምምነቱን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ ተቋም ቢግ ዊን ፊላንትሮፒ (Big Win Philanthropy) ጋር በይፋ ተፈራርመዋል።

የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ የከተሞች ከፍተኛ ዳይሬክተር ሄስቲንግስ ቺኮኮ በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የከተሞችን ትራንስፎርሜሽን የልማት እቅዷ ማዕከል ማድረጓ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አርአያነት ያለው ተግባር ነው።
ኢትዮጵያ የከተሜነትን ሂደት በታቀደ ስልት እና በጠንካራ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት እየመራች መሆኑ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
የአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ በከተሞች ስኬት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ጠቁመው፤ ከተሞች ለዜጎቻቸው ለሚሰጧቸው አገልግሎቶች ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዚህም ምርታማነትን ማሳደግ፣ ጥራት ያለው መሠረተ ልማት ማቅረብ እንዲሁም ፍትሐዊና ተደራሽ አገልግሎቶችን ማረጋገጥ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የያዘችው ጠንካራ የለውጥ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል፡፡
ይህ አዲስ የተፈረመው ስምምነት የሀብት ማሰባሰብ፣ የፋይናንስ አስተዳደር እንዲሁም የትራንስፎርሜሽን ጉዞውን ማፋጠን በሚሉ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተመላክቷል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025