የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወራቤ ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።

በስልጤ ዞን የተገነባው የሚቶ ኤድነባ መስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።



በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማእረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ኑርዬ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።


የውሃ አማራጮችን በመጠቀም የመስኖ ልማት በመተግበር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማጎልበት መቻሉን ጠቁመዋል።

ዛሬ ወደ ስራ የገባው የሚቶ ኤድነባ መስኖ ፕሮጀክት የዚሁ አካል መሆኑን አንስተዋል።

ከፍተኛ ወጪ ወጥቶባቸው የተገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲቆይ ህብረተሰቡ በተገቢው መንገድ መጠቀም እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ካሳዬ ተክሌ፤በተያዘው በጀት አመት በክልሉ 12 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል።


የሚቶ ኤደነባ የመስኖ ፕሮጀክትም በተያዘለት 6 ወራት ጊዜ ውስጥ ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ 54 ሄክታር ማሳ እንደሚያለማና 200 አባወራ እና እማወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

የከርሰ ምድር ውሀን በፀሃይ ሃይል በመሳብ ለመስኖ አገልግሎት እንዲውል የሚያደርገው ፕሮጀክቱ ከ105 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገበትም ገልጸዋል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፤ አርሶ አደሮች ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በዘመናዊ መንገድ አልምተው የቤት ውስጥ ፍጆታን በማሟላት ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች ላይ በማተኮር ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።


የመስኖ ፕሮጀክቱን ከሚጠቀሙ አርሶ አደሮች መካከል አቶ አብድልሰላም ሃሰን ከሁለት ሄክታር በላይ መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ ማልማታቸውን ተናግረዋል።

ሌላው አርሶ አደር ሃጅ ዋበላ ተማም በአራት ሄክታር መሬታቸው ላይ ሰብል እና አትክልት ማምረት መጀመራቸውን ገልጸው የመስኖ ፕሮጀክቱን በአግባቡ በመያዝ አገልግሎት እንዲሰጥ በተገቢው መንገድ እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል።


በእለቱም የወራቤ ከተማ አስተዳደር ውስጥ እየተከናወነ ያለው የ1 ነጥብ 6 ኪ.ሜ እንዲሁም ከሚቶ -ባራ- ቡልቡላ ድረስ እየተገነባ ያለው የ38 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ ያለበት ሁኔታ እንዲሁም የወራቤ ከተማ የወንዝ ዳርቻ ልማት ጉብኝት ተደርጓል።

በስነስርዓቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስልጤ ዞን የስራ ሃላፊዎች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026