🔇Unmute
ዲላ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል የትናንት ታሪካችን ብቻ ሳይሆን የነገ እድገትና አንድነታችን መሰረት ነው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ገለጹ።
ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ያሳዩትን አኩሪ ገድል የዘመኑ ትውልድ በልማቱ ሊደግመው ይገባል
130ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ" በሚል መሪ ሀሳብ በዲላ ከተማ ተከብሯል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ የዓድዋ ድል የሀገር ማንሰራራት የሚጸናበት የነጻነት ቀን ነው።
ዓድዋ ያለፈ የድል ታሪካችን ብቻ ሳይሆን የነገ እድገትና አንድነት መሰረት መሆኑን አንስተው፣ በአሁኑ ወቅትም ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የልማት ጉዞን ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።
ህብረ ብሔራዊነትን ለአብሮነትና ለሀገራዊ እድገት በመጠቀም በተለያዩ የልማት ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
በተለይ በክልሉ የሚገኙ ጸጋዎችን አቀናጀቶ በመጠቀም ከራስ ባለፈ ትርፍ አምራች የመሆን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ዓድዋ ጀግኖች አርበኞች የሕይወት መስዋዕትነት ጭምር ከፍለው የጥቁር ህዝብን ትርክት የቀየሩበት ደማቅ የጀግንነት ታሪክ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዲላ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ታሪኩ በየነ ናቸው።
ድሉ የነጻነትና የአንድነት ምልክት መሆኑን አንስተው እኛም ከዓድዋ ጀግኖች በመማር የድህነት ታሪካችንን መቀየር አለብን ብለዋል።
በዲላ ከተማ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በማጠናከር እድገትን ለማፋጠን በትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል በፓናል ውይይትና በተለያዩ ኪናዊ ዝግጅቶች የተከበረ ሲሆን ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የመከላከያ ሠራዊት አባላት ታድመዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025