የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የቡና ወጪ ንግድን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ለተቀናጀ ጥረት ትኩረት ተሰጥቷል

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የቡና ወጪ ንግድ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግና የቡና አቅርቦት ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን የግብርና ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ከቡና አምራቾች፣ ላኪዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በቡና ወጪ ንግድ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።


በውይይቱ ባለፉት ዓመታት በቡናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን በመገምገም፣ በቀጣይ ወራት ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡

የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምሰሶ የሆነውን የቡና ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው።

ተለዋዋጭ የሆነውን የዓለም ገበያ ታሳቢ በማድረግ የቡና ምርትን በጥራትና ፍጥነት ለገበያ ማቅረብ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፤ በቀጣይ ሦስት ወራት በአርሶ አደሮች፣ በአቅራቢዎችና ላኪዎች መጋዘን የሚገኘውን ቡና ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት ለዓለም ገበያ ማቅረብ አስፈላጊ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በተለይ ቡናን ጥራቱን በመጠበቀ ወደ ውጭ ለመላክ ርብርብ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ በዚህም የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ወደ አዲስ ከፍታ ለማድረስ የተቀናጀ ስራ ማከናወን እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

በቡና እሴት ሰንሰለት ውስጥ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች፣ አቅራቢዎችና ላኪዎች በእኩልነት ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር ይበልጥ እንዲጠናከር ይሰራልም ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ መድረክ ያለውን ተወዳዳሪነት ለማስቀጠል ከአርሶ አደሩ እስከ ውጭ ገበያ ያለው የጥራት ቁጥጥር ስርዓትን ይበልጥ ለማዘመን የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን የቡና ወጪ ንግድን በዓለም ገበያ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግና የቡና አቅርቦት ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ለተቀናጀ ጥረት ትኩረት መሰጠቱንም ተናግረዋል።

በተለይም የዓለም የቡና ዋጋ ሁኔታን በመከታተል ለባለድርሻ አካላት በየጊዜው ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር ማከናወን አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ በተለይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በፍጥነት እንዲቀርብ የተለያዩ ስራዎች እንደሚከናወኑ አመልክተዋል።


የኢትየጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት፤ በበጀት ዓመቱ 600 ሺህ ቶን ቡናን ወደ ውጪ በመላክ ሦስት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው፡፡

የተያዘውን ግብ ለማሳካትም የቡና አምራቾችና ላኪዎች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ መንግስትም ግቡን ለማሳካት ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የቡና ላኪዎች በሰጡት አስተያየትም፤ በመንግስት በኩል ዘርፉን ለማሳደግ የሚደረጉ የማሻሻያ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.