የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሸገር ከተማ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠሯል - ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሸገር ከተማ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ እና ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ላይ የሚታዩ መዋቅራዊ ችግሮችን በመፍታት በኩል ውጤታማ ሥራዎች እንዲመዘገቡ እያስቻለ ይገኛል፡፡

ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ከመተካት፣ የኤክስፖርት ገቢን ከማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከማሻሻል አንጻር እንዲሁም ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ አመርቂ ውጤት እያስገኘ ነው፡፡

የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ንቅናቄው በከተማው ኢንዱስትሪዎች በስፋት ወደ ሥራ እንዲገቡና ውጤታማ እንዲሆኑ ትልቅ አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ከምስረታው ጀምሮ ለአምራች ዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው የመሬት አቅርቦት ችግርን ከመፍታት ባለፈ፣ ለተጨማሪ ኢንቨስትመንት የሚሆኑ የማስፋፊያ ቦታዎች እንዲመቻቹ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

የግንባታ ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ሳይገቡ የቆዩ ባለሀብቶች በፍጥነት ወደ ግንባታና ወደ ምርት ሂደት እንዲሸጋገሩ መደረጉን ጠቅሰው በዚህም ከ800 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡

አምራቾች የብድር አቅርቦት እንዲያገኙ ከማድረግ አንጻር በዘንድሮው በጀት ዓመት ግማሽ ዓመት ብቻ 40 ቢሊየን ብር የሚጠጋ የብድር አቅርቦት መመቻቸቱን ከንቲባው አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በከተማዋ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን ጠቅሰው ሰፊ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር በወጪ ንግድ በኩልም አበረታች ውጤቶች እየተመዘገበ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡

በተጨማሪም ዘርፉ የከተማዋን የኢኮኖሚ መዋቅር በመደገፍ በኩል ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ከንቲባው አስታውቀዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግና ለባለሀብቶች ምቹ አካባቢን ለመፍጠር የሚነሱ ማነቆዎችን የመለየትና የመፍታት ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.