የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በአማራ ክልል የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ እየተደረጉ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ መጋቢት 1/2018( ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የገጠሩን ማህበረሰብ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት በማሳደግ አኗኗሩን ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ234 ሺህ 600 የሚበልጡ የኃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት መቻሉም ተገልጿል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ጥላሁን ሽመልስ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ የኃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል።

ቴክኖሎጂዎቹ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር በማዘመን ረገድ ያላቸውን የጎላ ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት በተለያዩ አማራጮች ስርጭት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

በዚህም ባለፉት ሰባት ወራት በተሰራ ስራ 100 ሺህ የሚደርሱ ኃይል ቆጣቢ ምድጃዎችን ለማሰራጨት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 109 ሺህ ያህሉን ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል።

እንዲሁም 54 ሺህ ኃይል ቆጣቢ የኤሌክትሪክ ምጣድና ምድጃዎች፣ ከ70 ሺህ 400 በላይ በፀሐይ ብርሃን ሃይል የሚሰሩ ለመብራትና መሰል አገልግሎት የሚውሉ ቴክኖሎጂዎችን ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።

በዚህም ለማገዶ ተብሎ የሚወድመውን የደን ምንጣሮ ለመከላከል ከማገዙም ባለፈ አርሶ አደሩ ባለበት ሆኖ የአማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉን አስረድተዋል።

ይህም ኃይል ለማግኘት በባህላዊ መንገድ ይደርስ የነበረውን የድካም፣ ኢኮኖሚያዊ ጫናና የጤና እክል ለመከላከል እንዳስቻለም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.