🔇Unmute
ባህር ዳር፤ መጋቢት 1/2018( ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የገጠሩን ማህበረሰብ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት በማሳደግ አኗኗሩን ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ234 ሺህ 600 የሚበልጡ የኃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት መቻሉም ተገልጿል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ጥላሁን ሽመልስ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ የኃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል።
ቴክኖሎጂዎቹ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር በማዘመን ረገድ ያላቸውን የጎላ ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት በተለያዩ አማራጮች ስርጭት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም ባለፉት ሰባት ወራት በተሰራ ስራ 100 ሺህ የሚደርሱ ኃይል ቆጣቢ ምድጃዎችን ለማሰራጨት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 109 ሺህ ያህሉን ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል።
እንዲሁም 54 ሺህ ኃይል ቆጣቢ የኤሌክትሪክ ምጣድና ምድጃዎች፣ ከ70 ሺህ 400 በላይ በፀሐይ ብርሃን ሃይል የሚሰሩ ለመብራትና መሰል አገልግሎት የሚውሉ ቴክኖሎጂዎችን ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።
በዚህም ለማገዶ ተብሎ የሚወድመውን የደን ምንጣሮ ለመከላከል ከማገዙም ባለፈ አርሶ አደሩ ባለበት ሆኖ የአማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉን አስረድተዋል።
ይህም ኃይል ለማግኘት በባህላዊ መንገድ ይደርስ የነበረውን የድካም፣ ኢኮኖሚያዊ ጫናና የጤና እክል ለመከላከል እንዳስቻለም አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025