🔇Unmute
አሶሳ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመኸር እርሻ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ግብርና ቢሮ የግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር ተስፋዬ በቀለ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ ለዘንድሮው የመኸር እርሻ የሚውል 131 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል።
እስከአሁን ድረስም 98 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በአሶሳ ከተማ እና መተከል ዞን በሚገኙ ማከማቻ መጋዘኖች እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአፈር ማዳበሪያው በወቅቱ መድረሱ አርሶ አደሩ የመኸር እርሻ ዝግጅቱን ከመጀመሩ በፊት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲያከናውን ጊዜ የሚሰጥ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ የአርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በየወረዳው በተደለደለው ኮታ መሠረት አርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያውን እንደሚወስድ ተናግረዋል።
ከአርሶ አደሩ በተጨማሪ በትልልቅ የእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች የአፈር ማዳበሪያ እንዲያገኙ በማድረግ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።
ከአፈር ማዳበሪያ በተጨማሪ የምርጥ ዘር ግብዓት በቅርቡ ወደ ክልሉ እንደሚገባም አረጋግጠዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026