🔇Unmute
አሶሳ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመኸር እርሻ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ግብርና ቢሮ የግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር ተስፋዬ በቀለ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ ለዘንድሮው የመኸር እርሻ የሚውል 131 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል።
እስከአሁን ድረስም 98 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በአሶሳ ከተማ እና መተከል ዞን በሚገኙ ማከማቻ መጋዘኖች እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአፈር ማዳበሪያው በወቅቱ መድረሱ አርሶ አደሩ የመኸር እርሻ ዝግጅቱን ከመጀመሩ በፊት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲያከናውን ጊዜ የሚሰጥ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ የአርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በየወረዳው በተደለደለው ኮታ መሠረት አርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያውን እንደሚወስድ ተናግረዋል።
ከአርሶ አደሩ በተጨማሪ በትልልቅ የእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች የአፈር ማዳበሪያ እንዲያገኙ በማድረግ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።
ከአፈር ማዳበሪያ በተጨማሪ የምርጥ ዘር ግብዓት በቅርቡ ወደ ክልሉ እንደሚገባም አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026