የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በጥራትና ፍጥነት እየተገነቡ ነው

Mar 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅግጅጋ፤መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በጥራትና ፍጥነት እየተገነቡ መሆኑን የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ፤ በጅግጅጋ ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን 1ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የታይዋን አስፋልት መንገድ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል።


የመንገዱ መገንባት የከተማዋን የተለያዩ አቅጣጫዎች የሚያገናኝ እና የትራንስፖርት ፍሰትን የሚያሳልጥ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም መንገዱ በተያዘለት ጊዜ በጥራትና ፍጥነት እየተከናወነ ስለመሆኑ በጉብኝታቸው ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።


በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች በጥራትና ፍጥነት እንዲጠናቀቁ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመሆኑም በከተሞችም ይሁን በገጠር ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026