🔇Unmute
ጅግጅጋ፤መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በጥራትና ፍጥነት እየተገነቡ መሆኑን የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ፤ በጅግጅጋ ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን 1ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የታይዋን አስፋልት መንገድ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል።

የመንገዱ መገንባት የከተማዋን የተለያዩ አቅጣጫዎች የሚያገናኝ እና የትራንስፖርት ፍሰትን የሚያሳልጥ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም መንገዱ በተያዘለት ጊዜ በጥራትና ፍጥነት እየተከናወነ ስለመሆኑ በጉብኝታቸው ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች በጥራትና ፍጥነት እንዲጠናቀቁ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመሆኑም በከተሞችም ይሁን በገጠር ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026