🔇Unmute
ሐረር፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን ዓለም አቀፍ ጫና ለመቋቋም በኃላፊነት መሥራት እንደሚገባ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ምሁር አስገነዘቡ።
በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር ፍሬዘር ጥላሁን፤ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ውስብስብ ችግር ለነዳጅ ገዢ ሀገራት ፈተና መሆኑን አንስተዋል።

ስለዚህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ነዳጅ ገዝተው የሚያስገቡ ሀገራት በቁጠባ መጠቀም እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል።
እንዲህ ዓይነት ዓለም አቀፍ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም በኤሌክትሪክ ኃይል ልማትና ተጠቃሚነት ላይ ማተኮር እንደሚገም አመላክተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ የልማት ጥረት ትልቅ ተስፋን የሠነቀ መሆኑን ጠቁመው፤ የአረንጓዴና ታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ማተኮሯ በጥሩ ተሞከሮነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት ጥረት እንዳለ ሆኖ ከነዳጅ ጋር በተያያዘ አሁን ያለውን ዓለም አቀፍ ችግር ለመሻገር በከፍተኛ ሀገራዊ አደራ እና የኃላፊነት ስሜት በትብብር መሥራት ይገባል ነው ያሉት።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026