🔇Unmute
ወልዲያ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በሰሜን ወሎ ዞን ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውሃን በመጠቀም የመስኖ ልማት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን የተቀረጹ የግብርና ፖሊሲዎችና አዳዲስ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው።
በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማትና በዘመናዊ የግብርና አሰራሮች የታየው ለውጥ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገር ያስቻለ ስለመሆኑ የተገኙ ውጤቶች ያመላክታሉ።
በከፍተኛ ትኩረት የተሰራው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን ስንዴ በሀገር ውስጥ ምርት መተካት ያስቻለ ታሪካዊ ስኬት ሆኖ ተመዝግቧል።
የእንስሳትና የዶሮ እርባታ፣ የማር ምርትንና የወተት ልማትን የሚያካትተው የ"ሌማት ትሩፋት" ኢንሼቲቭም የዜጎችን ተጠቃሚነትና የምርት አቅርቦት ለማሻሻል ያስቻለ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት በሁሉም አካባቢዎች በግብርና ልማት የተለያዩ አማራጭ ምርቶችንና ምርታማነትን የማሳደግ ጥረት በልዩ ትኩረት መከናወኑን ቀጥሏል።
ከዚህ አንፃር በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በተለይም በመስኖ ልማት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ኢዜአ የግብርና ባለሙያዎችንና አርሶ አደሮችን አነጋግሯል።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የመስኖ አግሮኖሚስት ወርቁ ደሳለ፤ በዞኑ የመስኖ ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ልማት ኢንሸቲቮች መልካም ውጤት እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ እና ሌሎችም ምርቶች ላይ የመስኖ አማራጮችን አስፍቶ በመጠቀም ምርታማነትንና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በዞኑ ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውሃን በመጠቀም የመስኖ ልማት በስፋት በማከናወን ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
በዚህም መሰረት በበጋው በ1ኛ ዙር ብቻ 32 ሺህ 525 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች በመስኖ ማልማት ስለመቻሉ ጠቁመዋል።
አጠቃላይ ምርቱ ሲሰበሰብ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በጉባላፍቶ ወረዳ የአላውሃ ቀበሌ አርሶ አደር ሞላ ገበየሁ እና በወረዳው ውድመን ቀበሌ አርሶ አደር መኮንን አርጋው፤ የምርት ግብዓቶችን በአግባቡ መጠቀም፤ በግብርና ባለሙያዎች ምክርና ድጋፍ ዓመቱን ሙሉ በምርት ሂደት ላይ ትኩረት አድርገን እየሰራን ውጤት እያመጣን ነው ብለዋል።
አርሶ አደሮቹ መሬታቸውን በበጋ መስኖ፣ በዝናብ ወቅት ደግሞ በመደበኛ የግብርና ስራዎች ላይ በማተኮር እንዲሁም በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026