የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመንግስት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ ለማድረግ እያገዘ ነው

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመንግስት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለመስጠት እያስቻለ መሆኑን የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።

ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በብሔራዊ ደረጃ የሚያገኙበት ሕጋዊና መሠረታዊ የመታወቂያ ዓይነት መሆኑም ይታወቃል።

የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ የቻለ ይግዛው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በየደረጃው ፈጣንና ፍትኃዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እያስቻለ ነው ።

በተለይም መታወቂያውን ከባንክና ሌሎች አሰራሮች ጋር በማስተሳሰር ወጥ የሆኑ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በፍትሃዊነት ለማቅረብ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በክልሉ ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከማስቻሉ ባሻገር ህገ- ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የራሱ ድርሻ እንዳለውም ጠቅሰዋል።

በተያዘው ዓመትም ከ4 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ነው ያመለከቱት።

ፋይዳ የዜጎች ትክክለኛ ማንነት የሚገልፅ መሆኑን አመልክተው ደሕንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026