የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ እንደሚገኝ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡

የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡


በዚሁ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ፤ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሪፎርም እርምጃ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነትን በማሳደግ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውም የኢትዮጵያና ጣሊያንን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር በማሳደግ በኃይልና በከተማ ልማት እመርታዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የጣሊያን አቻቸው አመራር ሰጪነትም የሀገራቱን የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር በማጠናከር ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የመሠረተ ልማትና የአሰራር ሥርዓትም አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ተመራጭነት እያጎለበተ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር፣ ሰፊ የገበያ ዕድልና የመንግስት ቁርጠኝነትም ቀጣናዊ የኢንቨስትመንት መዳረሻ የመሪነት ሚናዋን አጠናክራ እንድትቀጥል እያስቻላት መሆኑን ገልጸዋል።

ለብዝኅ የኢኮኖሚ ዘርፍ የተሰጠው ትኩረትም የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የንግድና ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም ኢትዮጵያ ከጣሊያን ጋር ያላትን ትብብር በማጠናከር ለቀጣናዊ ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።


የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያና ጣሊያን የሁለትዮሽ ግንኙነት በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተመሠረተ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያና ጣሊያን የታዳሽ ኃይል ልማት አቅምና የካበተ ልምድም ለሀገራቱ ትብብር ወሳኝ መሰረት መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉም ለጣሊያንና ዓለም አቀፍ አልሚዎች ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በምታካሂዳቸው የታዳሽ ኃይል፣ ሎጀስቲክስ፣ የአየር መንገድና መሰል መሠረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች በጣሊያን የማቴ ዕቅድ መሰረት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025

<p>የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት ይቀጥላል</p>

አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...

Feb 8, 2025