🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ እንደሚገኝ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡
የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

በዚሁ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ፤ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሪፎርም እርምጃ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነትን በማሳደግ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውም የኢትዮጵያና ጣሊያንን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር በማሳደግ በኃይልና በከተማ ልማት እመርታዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የጣሊያን አቻቸው አመራር ሰጪነትም የሀገራቱን የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር በማጠናከር ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የመሠረተ ልማትና የአሰራር ሥርዓትም አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ተመራጭነት እያጎለበተ እንደሚገኝ አንስተዋል።
የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር፣ ሰፊ የገበያ ዕድልና የመንግስት ቁርጠኝነትም ቀጣናዊ የኢንቨስትመንት መዳረሻ የመሪነት ሚናዋን አጠናክራ እንድትቀጥል እያስቻላት መሆኑን ገልጸዋል።
ለብዝኅ የኢኮኖሚ ዘርፍ የተሰጠው ትኩረትም የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የንግድና ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል።
በቀጣይም ኢትዮጵያ ከጣሊያን ጋር ያላትን ትብብር በማጠናከር ለቀጣናዊ ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።

የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያና ጣሊያን የሁለትዮሽ ግንኙነት በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተመሠረተ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያና ጣሊያን የታዳሽ ኃይል ልማት አቅምና የካበተ ልምድም ለሀገራቱ ትብብር ወሳኝ መሰረት መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉም ለጣሊያንና ዓለም አቀፍ አልሚዎች ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በምታካሂዳቸው የታዳሽ ኃይል፣ ሎጀስቲክስ፣ የአየር መንገድና መሰል መሠረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች በጣሊያን የማቴ ዕቅድ መሰረት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026