የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ገለጹ።

በ4ኛ 'ኢንቨስት በኢትዮጵያ' ፎረም ''ኢትዮጵያ ለቢዝነስ ዝግጁ ናት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።


በዚሁ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ፤ ኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነትን ለማሻሻል በትኩረት እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።

4ኛው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፎረምም የቢዝነስ ለቢዝነስ ትብብርን በማጎልበት የጋራ መግባባትና ትብብርን ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ የንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በወሳኝ የዕድገት ምዕራፍ ላይ እየተጓዘ ይገኛል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ለንግድና ኢንቨስትመንት አስቻይ ሥነ-ምኅዳር መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን እያበረታታ መሆኑን አብራርተዋል።

ለዚህም በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ ታዳሽ ኃይል፣ ማዕድንና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ሰፋፊ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን መክፈት ማስቻሉን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያን ስትራቴጂክ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የንግድና ኢንቨስትመንት ማዕከልነትን የሚያረጋግጥ የዕድገት ውጤት እያስገኘ መሆኑንም አንስተዋል።

በቀጣይም ዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶች ኢትዮጵያ የፈጠረቻቸውን ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ምኅዳር እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025