🔇Unmute
ሀላባ ቁሊቶ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በወተትና በዶሮ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመርሐ-ግብሩ ተሳታፊዎች ገለጹ።

ወጣት አብድልቃድር ሲራጅ እንደገለጸው፤ ከጓደኞቹ ጋር ተደራጅተው በተሠማሩበት የዶሮ ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ ሆነዋል።
በዚህም መሠረት አሁን ከ1 ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳላቸው እና በቀን እስከ 900 እንቁላል ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን አረጋግጧል።

ካፒታላቸው 3 ሚሊየን ብር ማለፉን እና ከ15 ለሚልቁ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም ገልጿል።
ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ አየለች ካሳ በበኩላቸው፤ በተሠማሩበት የከብት ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ በመሆን አሁን ላይ 10 የወተት ላሞችና 13 ጥጃዎች እንዳሏቸው ገልጸዋል።

በቀን ከ90 ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በእንስስት ሀብት ዘርፍ ያለውን ዐቅም ወደ ውጤት እንዲቀየር በማስቻል ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀላባ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ሀጂ ኑሪዬ ናቸው።

የዘርፉን ስኬታማነት ለማሳደግ ዝርያ የማሻሻል፣ የእንስሳት ጤና አጠባበቅና አመጋገብ ላይ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ከ17 በላይ የወተት፣ ከ21 በላይ የዶሮ እና ከ10 በላይ የማር መንደሮች መኖራቸውንም አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025