የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር ተጠቃሚ ሆነናል - የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ነዋሪዎች

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀላባ ቁሊቶ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በወተትና በዶሮ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመርሐ-ግብሩ ተሳታፊዎች ገለጹ።


ወጣት አብድልቃድር ሲራጅ እንደገለጸው፤ ከጓደኞቹ ጋር ተደራጅተው በተሠማሩበት የዶሮ ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ ሆነዋል።

በዚህም መሠረት አሁን ከ1 ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳላቸው እና በቀን እስከ 900 እንቁላል ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን አረጋግጧል።


ካፒታላቸው 3 ሚሊየን ብር ማለፉን እና ከ15 ለሚልቁ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም ገልጿል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ አየለች ካሳ በበኩላቸው፤ በተሠማሩበት የከብት ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ በመሆን አሁን ላይ 10 የወተት ላሞችና 13 ጥጃዎች እንዳሏቸው ገልጸዋል።


በቀን ከ90 ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በእንስስት ሀብት ዘርፍ ያለውን ዐቅም ወደ ውጤት እንዲቀየር በማስቻል ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀላባ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ሀጂ ኑሪዬ ናቸው።


የዘርፉን ስኬታማነት ለማሳደግ ዝርያ የማሻሻል፣ የእንስሳት ጤና አጠባበቅና አመጋገብ ላይ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ከ17 በላይ የወተት፣ ከ21 በላይ የዶሮ እና ከ10 በላይ የማር መንደሮች መኖራቸውንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025