የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር ተጠቃሚ ሆነናል - የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ነዋሪዎች

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀላባ ቁሊቶ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በወተትና በዶሮ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመርሐ-ግብሩ ተሳታፊዎች ገለጹ።


ወጣት አብድልቃድር ሲራጅ እንደገለጸው፤ ከጓደኞቹ ጋር ተደራጅተው በተሠማሩበት የዶሮ ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ ሆነዋል።

በዚህም መሠረት አሁን ከ1 ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳላቸው እና በቀን እስከ 900 እንቁላል ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን አረጋግጧል።


ካፒታላቸው 3 ሚሊየን ብር ማለፉን እና ከ15 ለሚልቁ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም ገልጿል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ አየለች ካሳ በበኩላቸው፤ በተሠማሩበት የከብት ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ በመሆን አሁን ላይ 10 የወተት ላሞችና 13 ጥጃዎች እንዳሏቸው ገልጸዋል።


በቀን ከ90 ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በእንስስት ሀብት ዘርፍ ያለውን ዐቅም ወደ ውጤት እንዲቀየር በማስቻል ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀላባ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ሀጂ ኑሪዬ ናቸው።


የዘርፉን ስኬታማነት ለማሳደግ ዝርያ የማሻሻል፣ የእንስሳት ጤና አጠባበቅና አመጋገብ ላይ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ከ17 በላይ የወተት፣ ከ21 በላይ የዶሮ እና ከ10 በላይ የማር መንደሮች መኖራቸውንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026