የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ወጣቶች የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ የኢትዮጵያን የወደፊት ዕጣ ፋንታ እንዲወስኑ በትምህርት ዝግጁ ማድረግ ያስፈልጋል

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ወጣቶች የዓለምን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት የሀገሪቷን የወደፊት ዕጣ ፋንታ እንዲወስኑ በትምህርት ዝግጁ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቆይታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የደረሰባቸውን አደጋ፣ የርዕዮተ ዓለምና የሀያላት አሰላለፍ ለውጥ፣ የቴክኖሎጂ ልህቀት በአፍሪካ ላይ የሚያመጣውን ተጽዕኖና ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ሚኒስትሩ በቆይታቸው የዓለም ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ነባራዊ ሁኔታ ለታዳጊ ሀገራት ፈታኝ መሆኑን በማንሳት፤ አስቸኳይና ወሳኝ ርምጃ ይፈልጋል ብለዋል፡፡

የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካውያን የህልውና ጥያቄ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን ለመቋቋም ስልታዊ እሳቤና ዝግጅት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡

ፈተናዎችን ተጋፍጦ ለድል የሚበቃ ትውልድ ለመፍጠር ለሁኔታዎች የማይበገር የትምህርት ስርዓት መገንባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ብሎም አፍሪካውያን ማድረግ የምንችለው ትልቁ ነገር የቀጣዩን ትውልድ በትምህርት በሚገባ ማዘጋጀት ነው ብለዋል፡፡

አፍሪካ በትምህርት ራሷን ለማዘጋጀት የቀጣዩን 50 ዓመት ልትጠቀምበት ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፤ በትምህርት ስርዓቱ ላይ መሰረታዊ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

የዓለምን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁሞ የኢትዮጵያን መፃኢ ዕድል ለመወሰን የተሟላ እውቀት፣ ብቁና ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መላመድ የሚችል ትውልድ መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ሪፎርም በማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን በማስፋፋት፣ የትምህርት መሰረተ ልማት በመገንባት፣ የሥርዓት ትምህርት ማሻሻያና ጥራት ማረጋገጫ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ይሄውም ቀጣዩን ትውልድ የማብቃት አካል መሆኑን ገልጸው፤ በራሱ የሚተማመን ሀገርን የሚጠብቅና አፍሪካ ወደፊት ሊደርስባት ከሚችል አደጋ የሚከላከል ዜጋ መፍጠር ያስችላል ብለዋል፡፡

ትምህርት የትውልድ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት የሰጡት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን ቀለል አድርጎ ማየት እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡

ትምህርት ወጣቶች የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ አመዛዝነው እንዲረዱና የሌሎችን ከመኮረጅ ይልቅ በሀገር በቀል እሳቤ አዳዲስ ሀሳቦችን እንዲያመነጩ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል፡፡

ለዚህም በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ በፖለቲካ፣ በፍልስፍናና በሌሎችም ዘርፎች ዓለም የሚያደርሰውን አሉታዊ ተፅዕኖ ተቋቁመው ማሻገር የሚችሉ ብቃት ያላቸው አመራሮችን ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ትምህርት ከአካዳሚክ እውቀት ባለፈ እሴቶችንና ማህበራዊ ንቃተ ህሊናን ማካተት እንዳለበት ገልጸው፤ ትምህርት ቀጣዩን ትውልድ ለማዘጋጀትና ለማስተማር ትምህርት የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የፖሊሲ አውጭዎች በወጣቶች ትምህርት ላይ መሰማራት የማህበራዊ ግብ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ ስትራቴጂያዊ ጉዳይ መሆኑን መረዳት አለባቸው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026