የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የዲጅታል ልማት ስትራቴጂ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት ነው

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቀሌ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የዲጅታል ልማት ስትራቴጂ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚከናወን ቀጣይነት ያለው ስትራቴጂክ ፕላን ይፋ በማድረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል።

የ2025 ስትራቴጂክ ተግበራ ስኬት ተደርገው ከሚወሰዱት መካከል የባንኮች የዲጅታል አገልግሎት መሳለጥ፣ የቴሌብር አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ፣ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና እና ሌሎችም ይገኙበታል።

የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ፤ የአዳዲስ ፈጠራዎች፣ የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በዲጅታል የታገዙ መሆናቸውም ለዘርፉ እድገትና ማንሰራራት ማሳያዎች መሆናቸውን መግለጽ ይቻላል።

ከዚህ ስኬትም በመነሳት የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋ ተደርጎ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ይገኛል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በትግራይ ክልል ያነጋገራቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በዲጅታል ልማት ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከባለሙያዎቹ መካከል ሰሎሞን ፀጋይ፤ በተለይም የቴሌብር አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ፣ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ለዘርፉ መሰረት ያኖሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የተቋማት የዲጅታል አገልግሎት እየተስፋፋ መምጣት ሌላኛው ስኬት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ከዚህ ስኬት በመነሳትም በቀጣይ አምስት አመታት የሚተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑን ገልጸዋል።

የድጅታል ቴክኖሎጂ ምርምርና ጥናት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሰሎሞን ገብረመድህን በበኩላቸው በተለይም ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው ለዘርፉ ልማትና አድገት ትልቅ አቅም መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እቅድን ለማሳከት ስልጠናዎች እንዳሉ ሆነው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የዘርፉ ባለሙያዎች በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ሌላኛው የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሀጎስ ገብረፃድቅ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ እንደ ሀገር የተከናወኑ ተግባራትና በቀጣይ የተያዙ እቅዶች የሚያጓጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በገጠርና በከተሞች የዲጅታል አገልገግሎትን በማስፋት ዜጎች ፈጣን፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከልም የዲጅታል ትግበራ የማይተካ ሚና የሚኖረው መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026